[the_ad_group id=”107″]

ስለ ዘፈን

Photo Credit: Dudu photography

ይህን ጽሑፍ ለማዘጋጀት ከመነሣቴ በፊት፤ ልጽፍ ያሰብሁበት ርእሰ ጕዳይ “ዘፈን” አልነበረም። ከዘፈን ጕዳይ በላይ የሚያሳስቡኝና እንደ የኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ቅድሚያ ሊሰጣቸው ይገባል ከምላቸው ጕዳዮች አንዱ በሆነው የቤተ ክርስቲያን ምንነት ላይ ነበር ዐሳቤን ማካፈል የፈለግሁት። ስለ ቤተ ክርስቲያን ጕዳይ ለዓመታት በውስጥ የሚነድድ ብርቱ ቅንዓት አለኝ። በዚህም ምክንያት የወንጌላውያን ቤተ እምነቶች አካሄድ እግዚአብሔር ለቤቱ ካለው ንድፍና ልብ እጅግ ርቆ፣ የሰው ሥርዐት ተጠናውቶት ያለበትን አካሄድ በተመለከተ የሚሰማኝን ለማጋራት ነበር አነሣሤ። ከሰፊው አማኝ ማኅበረ ሰብ ጋር በቶሎ እንዳልቀላቀል ከልክሎኝ የቈየውም ዋና ምክንያት ይኸው ነበር። ይህም ‘ከእሻላለሁ’ ባይነት በመነሣት ሳይሆን፣ ጌታ ኢየሱስን ወደ ማመን ከመጣሁበት ሁኔታ የተነሣ ነው። ጌታን መቀበል የቻልሁት ቤተ ክርስቲያን ‘ጠፉ’ ብላ ባገለለቻቸው ሙዚቀኞች በኩል ነበር። በዚህም ምክንያት እምነቴን እለማመድ የነበረው፣ መጽሐፍ ቅዱስን እንደ ጽኑ የእግዚአብሔር ድምፅ በመቀበል፣ የኅብረት አካሄድንም በቃሉ ላይ የነበረችውን የመጀመርያዋን ቤተ ክርስቲያን ምሳሌ በማድረግና ያንን ሕይወት ለመለማመድ በመሞከር ነበር። መሬት ላይ ያለው የቤተ ክርስቲያን አካሄድ ከቃሉ ከተረዳሁት ጋር ሊታረቅልኝ ሳይችል ከመቈየቱ የተነሣ የተቸገርሁትን መቸገር፣ ስለ ጌታና ስለ ቤቱ ፍቅር ስል ከነጥያቄዬም ቢሆን በግልጽ የተቀላቀልሁትንና እግዚአብሔር በሰጠኝ ጸጋ ለመታነጹ ራሴን ልሰጠውና፣ እኔም ልታነጽበት ለምወድደው ማኅበረ ሰብ ለማካፈል በማሰብ ነበር። ሆኖም ግን፣ ከተገኘሁበት ዓለምና ሳገለግል ከኖርሁበት ሙያ የተነሣ፣ አስቀድሜ አከራካሪውን የዘፈን ጕዳይ ማንሣት እንዳለብኝ አመንሁ። ይህን ስጽፍ ሊከተል የሚችለውን ተቃውሞና የፍርድ ውርጅብኝ ሳልጠረጥር ቀርቼ አይደለም፤ ነገር ግን፣ ጀግንነት (courage) ከፍርሀት ይልቅ በጎ ነውና ለበጎ ደፈርሁ።

ጌታን በሙዚቃ ሕይወት ውስጥ ማግኘት

አንዱ ጌታ ለወደደንና ለሞተልን ታናናሾች በተለያየ መንገድና ሁኔታ ራሱን ይገልጣል። በመንገዱ ላይ ሲያስጕዘንና በአንዱ በእርሱ እውነት ላይ ተመሥርተን ስንሄድም በተለያየ ፍጥነትና አካሄድ ነው። በእርሱ አንድ እንድንሆን እንጂ፣ አንድ ዐይነት እንድንሆን የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለም። እኔም እንደ አንድ ልትድን እንደ ታደለች ነፍስ፣ የእርሱ ምስክር ሆነው የወንጌልን እውነት ሊያካፍሉኝ የወደዱት ወንድሞች፣ በሰፊው አማኝ ማኅበረ ሰብ መረዳት “ቤተ ክርስቲያን” የሚሄዱና በዚያም በተለመደው መልኩ የሚያገለግሉ አልነበሩም፤ እንደውም “ዓለማዊ” ተብሎ የተፈረጀን ሙዚቃ በመጫወታቸው ምክንያት ከተቋማዊው ኅብረት የተገለሉ ነበሩ። እነኚህ ወንድሞች በርግጥ ዓለማዊ ሙዚቃን ተጫውተዋል፤ ከቤተ ክርስቲያን ርቀው በነበሩባቸው የመጀመሪያዎቹ ዓመታትም ፍጹም ዓለማዊ በሆነና ጠፉ በሚያስብል ዐይነት ሕይወት ዐልፈዋል። ሆኖም ግን፣ ለጥቂት ጊዜያት ተይዘውበት ከነበረው ክፉ አካሄድ ተላቅቀው፣ ራሳቸውን በቃሉ ጥናት እያተጕና እንደ ቃሉ ለመኖር፣ ብሎም ሌሎችንም ለመድረስ መለማመድን በጀመሩ ጊዜ፣ እንደ እኔ ላሉት መድረስ ችለው ነበር። ጌታን በእነርሱ በኩል ከማግኘቴ የተነሣ በቀጥታ የወረስሁት ወይም የተለማመድሁት የቤተ እምነት ሥርዐት ወይም ልማድ አልነበረም፤ ክርስትናንም የተረዳሁት ከአንድ የሃይማኖት ጎራ ከመመደብ በተለየ ነበር። በሕይወቴ የነበረው ለውጥ ከነበርሁበት የራስ ገዝ ሕይወትና አመለካከት፣ እግዚአብሔርን በቃሉ መሠረት ወደ መታዘዝ፣ እርሱን ወደ መምሰል ማደግና ወደ መሰጠት ሕይወት የመሻገር ነበር።

በዓለማዊነትና በዓለማዊ ሥርዐት ውስጥ እንዳሻው ይመላለስ ለነበረ ሰው ወደ እምነት መንገድ፣ ይህም የናዝሬቱ ኢየሱስ እርሱ ጌታ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ ወደ ማመን ለመጣ ማንኛውም ሰው ለውጡ ሥር ነቀል ይሆናል። ይህም ለውጥ ከጨለማ ወደ ብርሃን፣ ከሰይጣን ግዛት ዜግነት ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ዜግነት፣ ከራስ ፍቃድና ፍልስፍና ወደ አንድ የአምላክ ፈቃድ፣ ከኀጢአት ባርነት ወደ እግዚአብሔር ባርነት፣ ለምንወድደው ከመኖር እርሱ ለሚወድደው ወደ መኖር የሚደረግ የሕይወት ለውጥ ነው። እርሱ በሞቱ የሰጠንን ሕይወት እኛም ለፈቃዳችን በመሞት፣ በፍቃዱ በሕይወት ወደ መኖር የተሻግርንበትና እየተሻገርን የምንኖርበት ሕይወት ነው። እንግዲህ በዚሁ መረዳት ሙዚቃዊ አርቲስትነትም እንደ ማንኛውም ተግባርና ፍላጎት በእግዚአብሔር ቃል ሊመዘንና እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኝ መሆን አለመሆኑ ሊፈተሽ የሚገባው ነው። እኔም ወደ ክርስቶስ መንገድ በመጣሁ ጊዜ የነበርሁበትን ሕይወት በቃሉ ማስፈተሼ አልቀረም።

Photo Credit: Old Town Photography

ለእኔም ሆነ ዐብረን ቃሉን እንወድድ ለነበርን ወንድሞች፣ “ዘፈን” በቸልታ የተመለከትነው ጕዳይ አልነበረም። እግዚአብሔር በረዳን መጠን፣ በቻልነውም ልክ ዘፈንን በመላው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ተቀምጦ ያለበትንና በርግጥ ኀጢአት ሊሆን የሚችልበትን ሁኔታ በይስሙላ ጥረትና እንደ ታማነው በመንታ ልብ ሳይሆን፣ እውነትን ለማወቅና ባወቅነው እውነት ለመለወጥ በመፈለግ፣ በጾምና በጸሎት ጭምር ማስተዋልን ፈለግን።

ይህን ፍለጋ በጋራ ያካሄድነው ከሠላሳ የማያንስ አባላት በነበረውና ዘወትር ማክሰኞ ይሰበሰብ በነበረው፣ በአብዛኛው ሙዚቀኞችን ባቀፈው ኅብረት ውስጥ ነበር። በዚህ ኅብረት ውስጥ ከተለያየ ቤተ እምነት የመጣን ጌታን ፈላጊዎች ከየኖርንበት ወደ ቃሉ እውነት፣ ይህም በእግዚአብሔር ቃል በኩል የምንታረምበትና መንገዳችንን የምንቀይርበት እንጂ፣ እኛ እንደ ፍላጎታችን የምናርመው፣ መርጠን የምንቀበለው እንዳልሆነ ተማምነን፣ በዚያም እንደ ቃሉ ለመሠራት ራሳችንን የሰጠንበት ኅብረት ነበር።

ስለ ዘፈንም መልስን ከእግዚአብሔር በፈለግን ጊዜ፣ ከቃሉ በአንድ ክፍል ጌታ እንደ ተናገረን አምነን፤ በዚያው መሠረትም ቀሪውን የሙዚቃ አገልግሎታችንን ለመስጠት ጕዞን ጀመርን። ይህም ቃል፣ በገላትያ 5፥22-23 ላይ ያለው ክፍል ነበር። በገላትያ 5፥21 ላይ የተጠቀሰውን “ዘፋኝነት” ለመረዳት በምንተጋ ጊዜ መልስን ከሚቀጥለው ክፍል እንድናገኝ ሆነልን። “የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣ እምነት፣ የውሃት፣ ራስን መግዛት ነው። እንደነዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም።” (ገላትያ 5፥22-23)። በተለይም፣ “እንደነዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም” የሚለው ክፍል ደጋግሞ በውስጤ ሲሰማኝ አስታውሳለሁ፤ ለዓመታት በነበርሁበት መንገድ ላይ ይዞኝ የተጓዘውም ይኸው ቃል ነበር።

ይህን ጕዳይ ሳነሣ ለዘፈን ጥብቅና ልቈም ፈልጌ አይደለም። ይሁን እንጂ፣ እውነትን መናገርም ሆነ መነጋገር አስፈላጊ እንደ ሆነ ደግሞ አምናለሁ።

በኅብረቱ ውስጥ ለነበርነው ሙዚቀኞች ሕይወታችንና ሙዚቃችን በክፍሉ ውስጥ ለተጠቀሱት ባሕርያት መገለጫ እስከ ሆነና በቅዱሱ ቃል ላይ እስከ ተመሠረተ ድረስ፣ ሙዚቃዊ አገልግሎታችን የሥጋ ሥራ ሳይሆን፣ በዓለም ላይ ብርሃንና ጨው በመሆን የምንኖርበትን ኅብረተ ሰብ ከፍ ባለው ዕውቀትና ጥበብ የማነጽና የመገንባት ዕድልን የሚሰጠን መንፈሳዊ አገልግሎት እንደ ሆነ አምነን፤ በዚያም እምነት አዲሱን ምዕራፍ በዚያው በነበርንበት መንደር፣ በተለወጠና በየዕለቱ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ሊገራ በተሰጠ ማንነት ጀመርን። ምን ያህል ያሰብነውን አገልግሎት ባሰብነው ልዩነትና ቅድስና አከናወንን? ያንንስ ያለ መዋዠቅና ፍጹም ለእግዚአብሔር ዐሳብ በተሰጠ መንፈስ ማድረግ ችለን ነበር ወይ? ምን ያህል አፈራን? ምን ያህላችንስ የጌታ በመሆናችን ጸናን? እኛ የዚህ መንገድ ተጓዦች ለእነዚህ ጥያቄዎች የምንሰጠውም ምላሽ ብዙ የምንማርበት እንደሚሆን አምናለሁ። ሆኖም ግን፣ የተነሣንበት እውነትና የተበረታታንበት መንፈስ ፍጹም ቅን እንደ ነበር እመሰክራለሁ። በዚያም መንገድ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው ብዬ እስካመንሁበት ጊዜ ድረስ፣ እርሱ በረዳኝና ጸጋ ባበዛልኝ መጠን እንዳገለገልሁት እምነቴ ነው። እርሱ ያውቃል።

አማኝ እና ዘፋኝ

ኢትዮጵያ ውስጥ ባለን አማኞች መካከል አንድ ሰው ወደ መንፈሳዊነት ማዘንበሉን ወይም ከዓለማዊነት መላቀቁን ከሚገልጥባቸው ዋና ነገሮች መካከል፣ ዘፈን አለማድመጥ ወይም ሙዚቃ በሚቀርብባቸው ዝግጅቶች ላይ አለመታደም አንዱ ነው። ወደ እምነት የመጣው ሰው አስቀድሞ በሙዚቃ ሙያ ውስጥ የነበረ ከሆነ ደግሞ፣ ሙያውን ማውገዝና ከልምምዱ መውጣት የተለመደ ተግባር ነው። በወንጌላውያን አማኞች ዘንድ ዘፈንን በተመለከተ ያለው አመለካከት ከመጽሐፍ ቅዱሳዊነቱ ይልቅ ልማድ ላይ የተመሠረተ ይመስላል። ከእግዚአብሔር ዐሳብ በተቃራኒ ያሉ ብዙ ዓለማዊ ዕሴቶችንና አመለካከቶችን ዜማ ስለሌላቸው ብቻ እቅፍ ድግፍ አድርጎ የያዘ ማኅበረ ሰብ፣ በቅዱስ ቃሉ ላይ ግልጽ የሆነ ሙሉ ኵነኔ የሌለበትን የሙዚቃ ጕዳይ እንደ ጽድቅ መመዘኛ አድርጎ መውሰዱ ተገቢ ያልሆነ ብቻ ሳይሆን፣ ፍትሕ የጎደለው ሆኖ ይሰማኛል፤ በዚህም ፍርደ ገምድልነት ብዙዎች እንደተጎዱ አውቃለሁ።

ይህን ጕዳይ ሳነሣ ለዘፈን ጥብቅና ልቈም ፈልጌ አይደለም። ይሁን እንጂ፣ እውነትን መናገርም ሆነ መነጋገር አስፈላጊ እንደ ሆነ ደግሞ አምናለሁ። በዐጭሩ በሚያግባባን ቋንቋ ለመግለጽ፣ እኔ አሁን ዘፋኝ አይደለሁም። ስለ ዘፈን ለመጻፍ የተገደድሁት፣ እኔና እኔን መሰል ሙዚቀኞች ‘መብታችን ነው’ ባልነው መንገድ ስንሄድ የሚመለከቱን ወጣቶች፣ ‘የኢየሱስም የሙዚቃም መሆን ይቻላል’ የምንልበትን ዐሳብ ወይም ልብ ሳይረዱ በተሳሳተ ጎዳና እንዳይሄዱ ለማድረግ ነው። እኛን ተመልክተው እንደ ቃሉ ሳይሆን ለተጠላውና የኢየሱስ ለሆኑቱ ለማይገባው ዘፋኝነት የተጋለጡ ቢኖሩ፣ እነርሱን ለመመለስና አካሄዳቸውን የማስተካከል ዕድል ለመስጠት ነው። በሌላ አንጻር ደግሞ፣ የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት በተገቢው መንገድ ከመግለጽ ይልቅ፣ ከእግዚአብሔር በላይ ሰውን በመፍራትና ከተጠያቂነት ለመሸሽ ሲሉ፣ የብዙዎችን ጥያቄ በቸልተኝነት ሳያስተናግዱ በቀሩ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁራን፣ አገልጋዮችና የቤተ ክርስቲያን መሪዎች ምክንያት የተሰናከሉ ታናናሾች ቢኖሩ አቋሜንና መረዳቴን በማካፈል በጎ አስተዋጽዖ ለማበርከት ነው።

Photo Credit: Old Town Photography

እንደ እውነታው ከሆነ ይህን ርእሰ ጕዳይ አዳፍኖና ሸፈፍኖ ማለፍ የሚቻል አይመስለኝም። እውነትን በኀላፊነት መነጋገር ግን የተሻለ እንደ ሆነ አምናለሁ። ማናችንም ብንሆን የእግዚአብሔርን ቃል እንደየምቾታችን የመተርጐም መብት የለንም፤ ልናደርግ የምንችለው ቃሉን በቃሉና በመንፈሱ ተረድተን መልስን ለማግኘት መሞከር ነው። ምን ያህላችን በዚህ ጕዳይ ላይ እውነተኛ መልስን ለማግኘትና ትውልድን ለመታደግ እንጸልይ ይሆን? “ዘፈን ይወጋ! ይቀቀል! ይጠበስ!” የሚለውን ዐይነት ጸሎት አይደለም የምላችሁ፤ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነውን መልስ ከእውነታው በመፈለግ በፍጹም ልብ የሚደረግ ጸሎትን ማለቴ ነው።

እኔ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሁር ወይም የቋንቋ አዋቂ አይደለሁም፤ ነገር ግን እንደማንኛዋም የእግዚአብሔርን ፈቃድ ከቃሉ ለማስተዋል በየዕለቱ እንደምትተጋና አስተማሪው ቅባት ዐብሯት እንዳለ ሴት ከእርሱ የተማርሁትንና የምኖርበትን አካፍላለሁ። “እናንተስ ከእርሱ የተቀበላችሁት ቅባት በእናንተ ይኖራል፣ ማንም ሊያስተምራችሁ አያስፈልጋችሁም፤ ነገር ግን የእርሱ ቅባት ስለ ሁሉ እንደሚያስተምራችሁ፣ እውነተኛም እንደ ሆነ ውሸትም እንዳልሆነ፣ እናንተንም እንዳስተማራችሁ፣ በእርሱ ኑሩ።” (1ኛ ዮሐንስ 2፥27)

እግዚአብሔር በሙዚቀኞች መካከል ራሱን ከተቋማዊው አካሄድ ውጪ ሲገልጥና በእነርሱም ሊከብር ሲፈልግ፣ ከየትኛውም የወንጌላውያን ማኅበር ወይም አመራር ፈቃድ አላስፈለገውም፤ መንፈስ ቅዱስም በውስጣችን ለመኖር ከየትኛውም ሃይማኖታዊ ኮሚቴ ዕውቅናን አልጠየቀም። እግዚአብሔር የወደደውን እንደ ወደደ የሚያደርግ ትልቅ አምላክ ነው፤ እርሱ በሰዎች መካከል አድልዎን ሳያደርግ የሚያድን ደግ አምላክ ነው። ስለ ወደደና ስለ ራራልን አገኘን፤ ሌሎች በተቃወሙን ጊዜ ዐብሮ አልተቃወመንም፤ የሚሆንብንን ሁሉ ለበጎ እየለወጠ አበረታን፤ የበለጠ እንድንቀረጽበትና በትሕትና ለፍቃዱ እንድንሰጥ፣ የመታዘዝንም ደስታ እንድናውቅ ሠራን እንጂ። “. . . እግዚአብሔር ለሰው ፊት እንዳያዳላ፣ ነገር ግን በአሕዛብ ሁሉ እርሱን የሚፈራና ጽድቅን የሚያደርግ በእርሱ የተወደደ እንደ ሆነ በእውነት አስተዋልሁ።” (የሐዋርያት ሥራ 10፥34-35)

ይህ ሕዝብ የመዘመር እንጂ የመዝፈን ትእዛዝ ያልተሰጠው ሕዝብ ነው።

“ታዲያ አሁን ምን እናድርግ? ይህ ሁሉ ለምን አስፈለገ? እንዝፈን ለማለት ነው?” የሚል ጥያቄ ከተነሣ፣ ፍላጎቴ እንዝፈንም ሆነ አንዝፈን ለማለት ሳይሆን፣ የመዝፈንን ምንነት እንድንረዳ፤ በጌታ የሆነ ሙዚቃዊ አርቲስት አገልግሎቱን የት ድረስ መውሰድና ማሳደግ፣ ምንስ መጠበቅ ይችላል የሚለውን ወሳኝ ጥያቄ ዐብረን እንድንመልስ ነው። አዎ፤ ይህን መጠየቅ ወንጀልም ኀጢአትም አይደለም። በእኔ ዕይታ ወንጀል የሚሆነው እውነትን በሰው ፍርሀት ምክንያት አዳፍኖ ለማስቀረት የሚደረገው ጥረት ነው።

ዘፈን ምንድን ነው?

ዘፈን “ዘፈን” ነው የሚለው አባባል መልስ አይሆንም፤ ምክንያቱም በእግዚአብሔር ቃል ውስጥ የተጠቀሰባቸው ትርጕሞችና አገልግሎቶች ቃሉ አንድን ነገር ብቻ እንደማይወክል ያሳየናልና።

በእግዚአብሔር ቃል ዘፈን የሚለው ቃል በአንድ ዐይነት ትርጕምና በአሉታዊነት ብቻ አልተቀመጠም። በበዓልና በደስታ ጊዜ እንደሚደረግ ሙዚቃዊ ጨዋታና እንደ መንፈሳዊ (አምልኳዊ) ውዝዋዜ በአዎንታዊ ትርጕሙ የተገለጠ ሲሆን፣ በአንጻሩ ቅጥ ባጣ ስካርና በተጓዳኝ ባዕድ እንቅስቃሴዎች የተደገፈ ጭፈራና ፈንጠዝያን ለመግለጽ በአሉታዊ ገጽታውም ተጠቅሶ ይገኛል።

በዚህ ዘመን ዐውድ ዘፈን፣ ከእምነት ቤት አገልግሎት ይዘት ውጪ የሆነንና በተለያዩ ርእሰ ጕዳዮች ላይ፣ ስለ ጾታዊ ፍቅር፣ ስለ አገር ፍቅር፣ ስለ እናት ወይም አባት ፍቅርና ስለ ልጅ ፍቅር እንዲሁም ስለ ተለያዩ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ጕዳዮች የሚዜምባቸውን ሙዚቃዊ የጥበብ ሥራዎች ይወክላል። እነዚህ ሙዚቃዊ የጥበብ ሥራዎችና የታዳሚዎቹ የተሳትፎ ሁኔታ፣ ከሚከናወንበት ቦታና ሁኔታ ባሻገር፣ የሚተላለፈው መልእክት ከእግዚአብሔር ቃል አንጻር በሰዎች አእምሮ ላይ የሚፈጥረው ተጽዕኖ፣ እንዲሁም ስሜታቸው እንዲነሣሣ የሚያደርግበት አቅጣጫ ኀጢአት ነው ወይም አይደለም የሚለውን ጥያቄ የሚመልስ እንደ ሆነ አምናለሁ።

ስለ ጾታዊ ግንኙነት (ስለ ባልና ሚስት/እጮኛሞች ፍቅር) የተጻፈ ዘፈን ሁሉ ኀጢአት አይደለም። ጋብቻንና ጾታዊ ግንኙነትን በተመለከተ የሚቀርቡ የግንዛቤ ማስጨበጫ መልእክቶችን፣ የጽሑፍ እንዲሁም የፊልምና የቴሌቪዥን ሥራዎችን እያጣጣመ ለመከታተል ምንም ዐይነት ክልከላ የማይታይበት ሕዝብ፣ ተመሳሳይ ይዘት ያላቸው ሥራዎች በሙዚቃ ሲቀርቡለት ከኀጢአት አድርጎ የሚቈጥርበት መለኪያ ትልቅ ጥያቄን የሚፈጥር ሆኖ አገኘዋለሁ።

አንዲት ሴትና አንድ ወንድ በፍቅር ሕይወት ውስጥ ሲጓዙ፣ ግንኙነታቸውን የሚያጣፍጥ ገንቢነት ያላቸው የተለያዩ ነገሮችን ያደርጋሉ፤ ሙዚቃ በዚህ ውስጥ ያለው ሚና ከፍተኛ ነው፤ ይህንም በአማኙ ማኅበረ ሰብ ውሰጥ በቅርበት እንዳየሁት በስፋት ተጠቃሚ ያለው አገልግሎት ነው። ይህን ስመለከት “ሁሉም በየጓዳው የሚያደርገውን ነገር በአደባባይ እየወጣ የሚያወግዘው ማንን ፈርቶ ነው?” እያልሁ እጠይቃለሁ። እግዚአብሔርን? በፍጹም። እግዚአብሔርን የምንፈራበት ጕዳይ የአደባባይ ብቻ ሳይሆን የጓዳ ሕይወታችንንም ያካትታል። አማኙ ከዚህ አንጻር ዘፈንን በየመድረኩና በየሰዉ ፊት የሚያስረግመው ግብዝነትና ዐድር ባይነት እንደ ሆነ ተገንዝቤአለሁ። ይህን ስል ፈጽሞ ዘፈን የማይሰሙና ከልባቸው ተገቢ እንዳልሆነ አምነው በወጥ ማንንነት የሚመላለሱ አማኞች የሉም ማለት እንዳልሆነ ይታወቅልኝ፤ በርግጥም አሉና።

በአማኙ ማኅበረ ሰብ ውስጥ ስለ ጾታዊ ግንኙነት ያልሆኑ፣ በተለይ ስለ አገር የተዘፈኑ ዘፈኖችን ይዘታቸውና ጭብጣቸው ምንም ቢሆን ምን ከመዝሙር የመቍጠሩ ዝንባሌም ተገቢ አይደለም። የትኛውም የጥበብ ሥራ (ከሙዚቃዊ ጥበብ ውጪ ያሉትንም ጨምሮ) ሊዳኝ የሚገባው ከእግዚአብሔር ቃል አንጻር የሚያንጸባርቀውን እውነት በመፈተሽ ነው።

እኔ እንደተረዳሁትና መገንዘብ እንደቻልሁት፣ ዘፈን በዋናነት ኀጢአት ሆኖ የሚጠቀስበት የገላትያ 5፥21 ዐውድ የሚያመለክተው፣ ቅጥ ያጣና ልከኝነት የጎደለውን የሕይወት ዘይቤ በሙዚቃ ውስጥ መግለጽን ነው። ይህም ፍጹም ዓለማዊነትን የሚያንጸባርቅና የእግዚአብሔርን መኖር በዘነጋ መንፈስ የሚቀርብ ክንውን ሲሆን፣ ሥጋን በማስደሰት ላይ ባተኰረ አደራረግ የሚካሄድን ፌሽታና ገደብ የሌለው መዝናናትን የሚያመለክት ነው።

የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው፤ እርሱም ዝሙት፣ ርኵሰት፣ መዳራት፣ ጣዖትን ማምለክ፣ ምዋርት፣ ጥል፣ ክርክር፣ ቅንዓት፣ ቁጣ፣ አድመኛነት፣ መለያየት፣ መናፍቅነት፣ ምቀኝነት፣ መግደል፣ ስካር፣ ዘፋኝነት፣ ይህንም የሚመሰል ነው። አስቀድሜም እንዳልሁ፣ እንደዚህ ያሉትን የሚያደርጉ የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። (ገላትያ 5፥19- 21)

አማኝ ነኝ የሚል ሁሉ በማንኛውም ጊዜ እንደ መንፈሳዊ ሰው፣ በመንፈስ ሊመላለስ ይገባዋል። መንፈሳዊ ሰው ደግሞ እግዚአብሔርን ደስ የሚያሰኘውን በሁሉም ስፍራ የሚያደርግ ነው። በዚሁ መንፈስ ስንመላለስ፣ በመዝሙር ስም ስንዘፍን ከምንገኝባቸው ሁኔታዎችም ጭምር እንቆጠባለን ማለት ነው። እግዚአብሔር በልጁ በኢየሱስ ስም በሚሰበሰቡት ሕዝቡ መካከል መገኘትን የሚወድድ፣ በእውነትና በመንፈስ የሚመለክ አምላክ ነው። እርሱን በማምለክ ስም (ሽፋን) ሥጋችንን ለማስደሰት በምናደርገው ሁሉ እግዚአብሔር አይከብርም። ይህን ስል ስለ ሙዚቃ ዘውግና መሰል ገደቦች እያወራሁ አይደለም፤ ስለ እውነተኝነትና በፍጹም ልብ ሊሆን ስለሚገባው ሙዚቃዊ አገልግሎት እንጂ።

በዚሁ በገላትያ 5፥21 ላይ የተጠቀሰውን “ዘፋኝነት” ትርጕምን የሚጋራና የሚያሳይ ክፍል በዘፀአት ምዕራፍ ሠላሳ ሁለት ላይ ይገኛል። “ … ሕዝቡም ሊበሉና ሊጠጡ ተቀመጡ፤ ሊዘፍኑም ተነሡ።“ (ቍጥር 6)፤ “እርሱም፦ ይህ የድል ነሺዎች ወይም የድል ተነሺዎች ድምፅ አይደለም፤ ነገር ግን የዘፈን ድምፅ እሰማለሁ አለው። እንዲህም ሆነ፤ ወደ ሰፈሩ ሲቀርብ ጥጃውንም ዘፈኑንም አየ፤ የሙሴም ቁጣ ተቃጠለ …” (ቍጥር 18 – 19)

በቅዱስ ቃሉ ላይ ግልጽ የሆነ ሙሉ ኵነኔ የሌለበትን የሙዚቃ ጕዳይ እንደ ጽድቅ መመዘኛ አድርጎ መውሰዱ ተገቢ ያልሆነ ብቻ ሳይሆን፣ ፍትሕ የጎደለው ሆኖ ይሰማኛል፤ በዚህም ፍርደ ገምድልነት ብዙዎች እንደተጎዱ አውቃለሁ።

እስራኤላውያኑ ከግብፅ ባርነት ያወጣቸውን አምላካቸውን ረስተውና ወደ ጣዖት አምልኮ ዘወር ብለው፣ ለሥጋቸው ልቅነት በተመቸ ሁኔታ ውስጥ ከመብላትና መጠጣት ጋር፣ ከሩቅ ሊሰማ በሚችል የድምፅ ከፍታና ጩኸት ክብር ለማይገባው ክብርን ሲሰጡ የሚነበብበት ክፍል ነው። ዘፈን በተመሳሳይ ሁኔታ ያሉ ልምምዶችን የርኩሰት ተግባርን ሲያጅብና ሲመራ የሚገኝበት ሁኔታ አሁን ባለንበት ዘመንም እንደሚገኝ የታወቀ ነው።

እንዲህ ያለው “ዘፈን” ለባዕድ አምልኮ የሚውልና ዝሙት መሥዋዕት ሆኖ የሚቀርበብት ጭምር ነው። በተጨማሪም፣ በቀጥታ ከባዕድ አምልኮ ጋር ባልተገናኘ መልኩ ከልቅ የሕይወት ዘይቤና እርካታን ከማጣት የተነሣ፣ ስካርንና ልቅ የጋርዮሽ ወሲብን የሚያካትት ዐይነት ክፉ ተግባር የሚፈጸምበትም ነው። ዘፈንን በዚህ መልኩና ከዚህ ጋር ተያይዞ በሚኖረው ትርጕም ኀጢአት አይደለም ብሎ ሊከራከር የሚችል ሰው አለ ብዬ አላምንም። የሥጋ ሥራ ተብሎ እንዲኰነንና በእግዚአብሔር መንፈስ በሚመላለሱት መካከል ሊገኝ እንደማይገባ የተነገረው እንዲህ ያለው ልምምድ እንጂ፣ ዐሳብን በዜማና በሙዚቃ እጀባ የመግለጽ ጥበብ እንዳልሆነ ልናስተውል ይገባል።

በሌሎች የአዲስ ኪዳን መጻሕፍት ተጠቅሶ የምናገኘውም ከዚሁ ዐውድ አንጻር ነው። “በቀን እንደምንሆን በአግባብ እንመላለስ፤ በዘፈንና በስካር አይሁን፣ በዝሙትና በመዳራት አይሁን፣ በክርክርና በቅናት አይሁን።” (ሮሜ 13፥13) “የአሕዛብን ፈቃድ ያደረጋችሁበት በመዳራትና በሥጋ ምኞትም በስካርም በዘፈንም ያለልክም በመጠጣት ነውርም ባለበት በጣኦት ማምለክ የተመላለሳችሁበት ያለፈው ዘመን ያበቃልና።” (1ኛ ጴጥሮስ 4፥3)።

ዘፋኝነት ከላይ በተጠቀሱት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ላይ ከተቀመጠበት ዕይታ አኳያ፣ በጋርዮሽ ወሲብና በጣዖት አምልኮ (orgy) ውስጥ እስካልተሳተፍን ድረስ ለመለማመድ ነጻ የሆነ ተግባር አድርገን እንድናስብ የሚያስችለንም አይደለም። ማንኛውም ልቅ የሆነና ከፈሪሃ እግዚአብሔር የራቀ የመዝናናት ልምምድ፣ ከሙዚቃ ጋርም ሆነ ያለ ሙዚቃ የሥጋ ሥራና የክርስቶስ ለሆኑት የማይገባ እንደ ሆነ አስረግጠን ልንረዳ ይገባል።

Photo credit: Tedos Teffera

የክርስቶስን ዳግም ምጽዓት በተስፋ የሚጠባበቀው ሕዝብ አምላኩን ለመምሰል ራሱን እያስገዛ የሚኖር ነው። ይህንም ሲያደርግ፣ እንደ መንፈስ ቅዱስ ፈቃድ የተሰጠውን ስጦታ በጨለማ ላሉት ወደ ብርሃን መምጣት፣ በቤቱ ላሉት መታነጽ እንዲሁም በሚኖርበት ኅብረተ ሰብ በጸጥታና በዝግታ፣ በሰላምና በሰማያዊ ፍቅር በመመላለስ ነው። ይህ ሕዝብ የሞተለትን ጌታ በመግለጥ ስሙን የሚያስከብር ልከኛ ሕዝብ እንጂ፣ በዓለም ያሉቱ ሁሉ የሚያደርጉትን የሚያደርግ፣ በተድላና በፌሽታ ጕዳይ የተያዘ ሕዝብ አይደለም። ይህን የሚያደርገውም ባለመዝፈን ብቻ ሳይሆን በልምምዶቹ ሁሉ ነው። ሲበላ፣ ሲጠጣ፣ ሲለብስ፣ ሲነግድ፣ ሲወዳጅ፣ ሲያገባ፣ ሲያገለግልና በመሳሰሉት ሁሉ የዓለም ቤተኛ ሆኖና መስሎ ሳይሆን፣ በዚህ ምደር እንደ ባይተዋርና እንደ መጻተኛ ፍጹሚቱን አገሩን እየናፈቀና እየሰበከ የሚኖር ሕዝብ ነው። ይህ ሕዝብ የመዘመር እንጂ የመዝፈን ትእዛዝ ያልተሰጠው ሕዝብ ነው። “በመዝሙርና በዝማሬ በመንፈሳዊም ቅኔ እርስ በርሳችሁ ተነጋገሩ፤ ለጌታ በልባችሁ ተቀኙና ዘምሩ።” (ኤፌሶን 5፥19)

ይሁን እንጂ፣ ከዚህ ሕዝብ መካከል እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሙዚቃ ተሰጥኦ ያላቸው ቢኖሩና ያንንም በጌታ ባመኑትም ሆነ፣ ባላመኑት ፊት ሊከውኑ እንደ ተሰጣቸው ተረድተው በታማኝነት ቢያገለግሉ፣ ሥራቸው በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በዝማሬ የሚቀርብ አምልኮ ባለመሆኑ ዓለማዊ አይሆንም። የአገልግሎቱ ስያሜ ዘፈንም ይሁን መዝሙር፣ የሚቀርብበት መንፈስና የሚያነሣው ዐሳብ እግዚአብሔር የሚከብርበት ይሁን ወይም አይሁን የሚወስነው ይሆናል።

በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ ወዳጆች ጋር ኢየሱስ በሠርግ ቤት ወይም በተመሳሳይ የባሕላዊ ጨዋታዎች ቦታ በሚገኝ ጊዜ የሚኖረው አኳኋን እንዴት ይመስላችኋል የሚለውን ጥያቄ እንጠይቃለን። የሚመስለንን ስንነጋገር የምጠይቀው ጥያቄ፣ ̕‘ኢየሱስ ሠርግ ቤት ሲታደም ዘፈን አለ ብሎ ይጨነቅ ይሆን? ወይስ ደስ ብሎት የሚጫወቱትን ይመለከት ይሆን? የሙዚቃው ምት ይነሽጠው ይሆን? እግሮቹ በተቀመጠበት የሙዚቃውን ምት ተከትለው ይንቀሳቀሱ ይሆን? እንደ ማንኛውም ታዳሚ ከሰዉ ጋር ተቀላቅሎ በደስታ ይጫወት ይሆን? ወይስ ሁሉን እንደ አግባቡና እንደየሁኔታው ያስተናግድ ነበር?’

እርሱን በማምለክ ስም (ሽፋን) ሥጋችንን ለማስደሰት በምናደርገው ሁሉ እግዚአብሔር አይከብርም።

እኔ የማውቀው ኢየሱስ ሁሉን እንደ አግባቡና ሁኔታው የሚያስተናግድ፣ ባሕላዊ ጨዋታዎች ላይ መገኘትና የሚጫወቱትን ሰዎች ደስታ መታደም ደስ የሚያሰኘው፣ እየቀረበ ያለ ሙዚቃዊ ትርኢት ቢኖርና በዚያ ላይ ጥሩ አጨዋወትና የተለየ ተሰጥኦ ቢገጥመው በአድናቆት የሚያጨበጭብ ይመስለኛል። ምን አልባት ዐብሯቸው እንዲጫወት ግድ ቢሉት እንኳ ስለ ግብዣቸው በጥቂቱም ቢሆን ጠጋ ብሎ አጫውቷቸው ወደ መቀመጫው የሚመለስም ይመስለኛል። ኸረ እንደውም፣ ‘በደንብ ዐብሯቸው ይጫወታል’ የምትሉም ትኖራላችሁ። ከኀጢአት በቀር በሁሉ እንደ እኛ ሰው ነውና ሊሆን ይችላል። እኔ የተረዳሁበትና ያየሁበት ልክ ይህን ያህል ነው። እኔም እንደ አማኝ የማደርገውና ላደርግም የማስበው፣ ቢደረግም የተሻለ ነው የምለውም በዚህ መልኩ የሆነውን አያያዝ ነው። የትኛውም ሰባኪና አስተማሪ፣ ሠርግ ቤት ሄጄ “ሙሽሪት ሙሽራው እንኳን ደስ አላችሁ” በሚል ዘፈን የሚጫወትን ቤተ ዘመድና ወዳጅ አጅቤ ባጨበጭብ፣ በጥቂቱም በጨዋታው ብሳተፍ (ሌሎችን ላለማሰናከል በሚለው ዕሳቤ ራሴን እቆጥብ ይሆናል እንጂ)፣ ‘ኀጢአት ሠራሽ’ ወይም ‘ሥጋሽን ያለ አግባብ አስደሰትሽ’ በሚል ወቀሳ መንፈሳዊነቴን ጥያቄ ውስጥ ቢያስገባ የምቀበለው አይሆንም።

በመጽሐፍ ቅዱሳችን ዘፈን ሰዎች ደስ በተሰኙ ጊዜ እንደሚያደርጉት ያለ አዎንታዊ ተግባርን ወክሎ ተቀምጧል፤ ከዚህ ውስጥ ዋነኛ ምሳሌ ሊሆን የሚችለው ጌታ ኢየሱስ በሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 15 ላይ በጠፋው ልጅ ምሳሌ የተጠቀመው ነው።


ይህ ልጄ ሞቶ ነበርና ደግሞም ሕያው ሆኖአል፤ ጠፍቶም ነበር ተገኝቶአልም። ደስም ይላቸው ጀመር። ታላቁ ልጁ በእርሻ ነበር፤ መጥቶም ወደ ቤት በቀረበ ጊዜ የመሰንቆና የዘፈን ድምፅ ሰማ፤ ከብላቴናዎችም አንዱን ጠርቶ፦ ‘ይህ ምንድን ነው?’ ብሎ ጠየቀ። እርሱም፦ ‘ወንድምህ መጥቶአልና በደኅና ስላገኘው አባትህ የሰባውን ፍሪዳ አረደለት’ አለው። (ሉቃስ 15፥24-27)

ጌታ ኢየሱስ የዘፈንን ጕዳይ በቀጥታ የተናገረበት ቦታ ባይኖርም፣ በዚህ ምሳሌው ውስጥ ዘፈን የሚለው ቃል፣ የደስታ መግለጫ ሙዚቃንና ጨዋታን ወይም በዓልን የሚወክል ሆኖ በበጎ ጎኑ ተቀምጧል።

በተመሳሳይ ሁኔታም በተለያዩ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍት ተጠቅሶ ይገኛል። ለዚህ የሚከተለው በንጉሥ ሰሎሞን የንግሥና በዓል ወቅት የነበረውን ደስታ የሚገልጠው ክፍል ጥሩ ምሳሌ ይመስለኛል። “ሕዝቡም ሁሉ እርሱን ተከትለው ወጡ፣ ሕዝቡም ዘፈን ይዘፍኑ ነበር፣ በታላቅም ደስታ ደስ አላቸው፤ ከጩኸታቸው የተነሣ ምድር ተናወጠች።” (1ኛ ነገሥት 1፥40)

በዚህ ክፍል ላይ እግዚአብሔር በዘመኑ ያደርግ እንደ ነበረው በነቢይ፣ “ስለ ምን ዘፈናችሁ?” በማለት መልእክትን ወደ ንጉሥ ሰሎሞንና ወደ እስራኤል ሕዝብ አልላከም፤ በንስሐ ይመለሱ ዘንድ ቁጣውንም አልገለጠም። ምክንያቱም በንጉሥ ሰሎሞን የንግሥና በዓል ወቅት የነበረው ዘፈን እንደ ፈቃዱ የሆነ ስለ ነበር።

ሌላው “ዘፈን” የሚለው ቃል እግዚአብሔርን የማምለክ ተግባርን ለመግለጽ ሲውል የሚያሳዩት የመዝሙረ ዳዊት ክፍሎች ናቸው። በእነዚህ ክፍሎች ላይ ዘፈን ለእግዚአብሔር የሚቀርብን በደስታ የተሞላ ምስጋናን ለመገለጥ የሚያገለግል ቃል ሆኖ እናያለን። “ስሙን በዘፈን ያመስግኑ፣ በከበሮና በመሰንቆም ይዘምሩለት።” (መዝሙር 149፥3) “በከበሮና በዘፈን አመስግኑት፤ በአውታርና በአምቢልታ አመስግኑት።” (መዝሙር 150፥4)

የእኔ መሻትና ጥልቅ ፍላጎት እግዚአብሔርን ማክበር ነው። ይህንም እርሱ በወደደው መልኩ፣ በሰጠኝ ስጦታና አቅም ሁሉ ላደርግ እወድዳለሁ። ስለ ዘፈን እየሞገቱ መኖር የሕይወቴ ዐላማ አይደለም፤ ዘፈን መዝፈን የሚቻልበትና የማይቻልበት ሁኔታና አግባብ ቢኖርም ባይኖርም፣ ከዚህ በኋላ የእኔ ጕዳይ አይደለም። የምፈልገው እግዚአብሔርን በሁለንተናዬ ማምለክ ነው። የጌታ የሆኑትም ሁሉ የጊዜውን መክፋት እያዩ፣ ሰዎችን ሁሉ የሚወድደውንና አንድ ልጁን የሰጠውን እግዚአብሔርን በማወቅ፣ ካለውና ከሚመጣው ክፉ እንዲያመልጡ ነው። እነዚህም በነገር ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስን በመግለጥ ቢተጉ በዚህ እግዚአብሔር እንደሚከብር አምናለሁ።

ለጥበበኞቹ

በሙዚቃዊ ጥበብ ሊገፉ ለሚወድዱ ሁሉ ማለት የምፈልገው፦ እንደ እግዚአብሔር ቃልና ፈቃድ ብታደርጉት የሚከለክላችሁ ሕግ የለም፤ ነገር ግን፣ ‘ማድረግ የምችለው የተሻለው ነገር ይህ ነው ወይ?’ ብላችሁ ከመጠየቅ ጀምሩ። ‘እግዚአብሔር ብርሃኑን በጨለማው ዓለም ላይ ይገልጥ ዘንድ የመረጠልኝና ሊከብርብኝ የወሰነው መንገድ ይህ ነው ወይ?’ ብላችሁ አጥብቃችሁ ጠይቁ፤ ጸልዩ።

የሙዚቃ ሥራችሁን ለማቅረብ በምትሰማሩበት ቦታ ልዩነታችሁ በሥራችሁ ይዘት፣ በበጎ የሕይወት ምስክርነትና ዓለምን ባለመምሰል ይሁን። ሥራችሁን የምታቅርቡበትን ቦታና ሰዓት ጭምር ለማስጠበቅ የምትችሉትን ሁሉ አድርጉ። በአንዳንድ ሁኔታ እግዚአብሔር፣ ለእርሱ ዐላማ እቈማለሁ ብላችሁ በማታስቡበት ስፍራ ላይ ስሙን ሊያስጠራ ይልካችሁ ይሆናል። ከዚያ ውጪ ግን ሰዎች ሙዚቃችሁን በሚመስላችሁ ቦታ እንዲታደሙ ተጠንቅቃችሁ መሥራት ይኖርባችኋል። በጋራ የሚቀርቡ የሙዚቃ ድግሶችን ተመሳሳይ ዕሴትን ከምትጋሯቸው ጋር ብቻ አድርጉ።

Photo Credit: Bereket Tamiru

የምሽት ክበቦች ዘፈን በአሉታዊ ትርጕሙ የሚገለጥባቸውና የሚከወንባቸው ናቸውና እግራችሁን ሰብስቡ። በዚያ ሙዚቃ ለስካር ድግስና ለዝሙት ቀጠሮ አጃቢ ሆኖ እንጂ፣ ዋናው ጕዳይ ሆኖ አይስተናገድም። የሙዚቃን ጥበብ ዋናው መስሕባቸውና ጕዳያቸው አድርገው የሚንቀሳቀሱ ክበቦች ቢኖሩ (ቢገጥሟችሁ) ትርኢታችሁን የምታቀርቡበትን ሰዓት በመገደብ ልታገለግሉ ትችላላችሁ።

በሙዚቃዊ ጥበብ ሊገፉ ለሚወድዱ ሁሉ ማለት የምፈልገው፦ እንደ እግዚአብሔር ቃልና ፈቃድ ብታደርጉት የሚከለክላችሁ ሕግ የለም፤ ነገር ግን፣ ‘ማድረግ የምችለው የተሻለው ነገር ይህ ነው ወይ?’ ብላችሁ ከመጠየቅ ጀምሩ።

መርሳት የሌለባችሁ ቍም ነገር፣ እንዲያገለግሉት ሳይሆን ሊያገለግል የመጣው ጌታ ደቀ መዝሙር ነኝ የሚል የትኛውም ሰው፣ ያንኑ የአገልጋይነት ማንነት በሄደበት ስፍራ ሁሉ ሊያንጸባርቅ የሚገባው መሆኑን ነው። በዓለም ያሉት ሁልጊዜ ከፍ ያለ ቦታን ይሻሉ፤ ለእኛ ግን ከፍታ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መኖር ነው። ስለዚህም ትልቅና ክቡር በሚመስሉ ስፍራዎች ብቻ ሳይሆን፣ ሰዎችን የእውነት ለማገልገልና ጌታን ለማስከበር ዕድል በሚሰጡ አጋጣሚዎች ሁሉ ተጠቅማችሁ እንድታገለግሉ እመክራለሁ።

የመሣሪያ ተጫዋቾች በአንድነት ተደራጁ፤ ተነጣጥላችሁ ከእግዚአብሔር እውነት እጅግ የራቀ ዐሳብ የሚሸጡ ዓለማውያን ዘፋኞችን በማጀብ ከጨለማ ጋር አትተባበሩ። ምናልባት እግዚአብሔርን የሚፈሩና በጎ ዐሳብን ለትውልድ የሚያጋሩ ጥቂቶችን ብታገኙ እያስተዋላችሁ ተሳተፉ። ነገር ግን፣ ድምፅን ጨምሮ በአንድ ዐላማና መንፈስ ለበጎ ተጽዕኖ የሚሆኑን፣ ከዓለማዊነት የራቁና እንደ እግዚአብሔር ቃል የሆኑ ሥራዎችን እየጻፋችሁ ብትሠሩ ያልተበረዘ ንጹሕ ተጽዕኖን መፍጠር እንደምትችሉ አምናለሁ።

ሙዚቃዊ ጥበብን ከፈሪሃ እግዚአብሔር ጋር ዐብሮ ማጣጣም የሚችለው ታዳሚም በጣም ውስን እንደ ሆነና ከዚህም የተነሣ ለሙዚቃ ባለሙያው የሚኖረው ኢኮኖሚያዊ ጥቅም እንዲሁ ውስን እንደ ሆነ ማወቅና፣ ዐውቃችሁ መግባትም በጣም አስፈላጊ ይመስለኛል።

ዘፈንን (ሙዚቃዊ ጥበብን) በልዩነትና እንደ እግዚአብሔር ቃል ለመከወን የሚደረገው ሙከራ ዋጋን የሚያስከፍልና መሥዋዕትነትን የሚጠይቅ በመሆኑ፣ አስቀድመን በርግጥ ለእኛ የታየልንና እግዚአብሔር የሚፈልገን በዚያ አገልግሎት ውስጥ እንደ ሆነ በሚገባ መረዳት ይኖርብናል። የእግዚአብሔር ፈቃድ ከሆነ ይከብርበታልና፣ ዋጋም ቢከፈልለት ያዋጣል። ፈቃዱ መሆኑን ርግጠኞች ካልሆንን ግን፣ በዚያ መንገድ ከመጓዝ ብንቆጠብ በጣም የተሻለ ይሆናል። አሊያ ግን ዋጋ የሚያስከፍሉ ሁኔታዎችን ለማምለጥ ስንሞክር ከቈምንበት እውነት እየተንሸራተትን፣ ዓለምን ወደ መምሰል ልንሄድና ከዐላማችን ውጪ በሆነ አገልግሎት ልንጠመድ እንችላለን።

በዓለም ያሉት ሁልጊዜ ከፍ ያለ ቦታን ይሻሉ፤ ለእኛ ግን ከፍታ የእግዚአብሔርን ፈቃድ መኖር ነው።

ሌላው እንድትጠነቀቁ ማሳሰብ የምፈልገው ከሰዎች ምስጋና ነው። ጌታ ኢየሱስ በሰዎች እንዳልተማመነባቸውና ክብርንም ከሰው እንዳልተቀበለ ሁሉ፣ የእርሱ የሆኑም ክብርንም ሆነ ምስጋናን ከጌታቸው ብቻ ሊጠብቁ ይገባቸዋል። የጌታ የሆኑት ሁሉ ሰውን ሳይሆን እግዚአብሔርን ሊያስደስቱ የሚገባ ነውና። ሰውን የምናስደስት ቢሆን እንኳን ልናስደስት የሚገባው እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ነው። የሰዎች ጭብጨባ ወጥመድ ውስጥ የሚያስገባና ለእግዚአብሔር ፈቃድ ታማኝ ከመሆን የሚያሰናክል በመሆኑ፣ ከተነሣችሁበት ንጽሕና ራሳችሁን ርቃችሁ እንዳታገኙ በነቃ መንፈስ መመላለስ ግድ ይላችኋል። “ሰውን ወይስ እግዚአብሔርን አሁን እሺ አሰኛለሁን? ወይም ሰውን ደስ ላሰኝ እፈልጋለሁን? አሁን ሰውን ደስ ባሰኝ የክርስቶስ ባሪያ ባልሆንሁም።” (ገላትያ 1፥10)

የክርስቶስ ለሆኑት ሁሉ፣ የክርስቶስ ባሪያ ከመሆን ውጪ አማራጭ የላቸውምና ሁሉ ለእርሱ ደስታ፣ ሁሉ ለእርሱ ክብር፣ በማንኛውም ቦታም ይሁን ሁኔታ ሊደረግ የተገባ ነው። “እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት።” (1ኛ ቆሮንቶስ 10፥31)

እግዚአብሔር ልጆቹን ይምራ!

Zeritu Kebede

” ‘መንፈስ ቅዱስ ካልተናገረ እኔ የምነግራችሁ አንዳች የለም’ ብሎ ጉባኤውን ማሰናበት ጤናማነት ነው”

መጋቢ መስፍን ሙሉጌታ በኮልፌ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን በመጋቢነት ያገለግላሉ። ከዚህ በተጨማሪ፣ ዘወትር ዓርብ ቤተ ክርስቲያኒቱ በምታዘጋጀው “የፈውስና ነጻ የማውጣት” መርሓ ግብር ላይ ላለፉት በርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል። በዚህ ዘመን በፈውስ ስጦታ ቤተ ክርስቲያንን ያገልግላሉ ከሚባሉት አገልጋዮች መካከል የመጋቢ መስፍን ስም ቀድሞ ይነሣል። ሕንጸት ስለ መንፈስ ቅዱስ፣ ስለ ስጦታዎቹ እና አጠቃቀሙ እንዲሁም ከዚሁ ጋር ተያይዘው ስለሚነሡ ጉዳዮች ከመጋቢ መስፍን ሙሉጌታ ጋር ያደረገው ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል።

ተጨማሪ ያንብቡ

“እስሮችን ዐስቡ”

በግንብ፣ በብረት፣ በአደገኛ እሾሃማ አጥር፣ ጠብ መንጃ በታጠቁ ወታደሮች የሚጠበቅ ቅጥር ግቢ፣ ወደ ጎን ግድግዳ፣ ወደ ላይ ሰማይ ብቻ የሚታይበት የጽልመት ዓለም፣ የቁጭት ማእበል የሚንጠው አእምሮ፣ ‘ምነው ባላረኩት ኖሮ’ የሚል የጸጸት ወላፈን የሚለበልበው ልብ፣ ፍትሕን ሳታገኝ በግፍ የተከረቸመች ነፍስ፣ ከሚወዱት ቤተ ሰብ፣ ጓደኛና ከማኅበረ ሰብ ተገልሎ በሚገኝ ጠባብ ዓለም ውስጥ የተስፋን ቀን እየጠበቁ መኖር፣ ወዘተ. የወህኒ ሕይወት አንዱ አካል ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ

78 comments

Leave a Reply to Killa L Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

  • it is really true. this is it. any body who wants to know about music (Zefen) ,go to Holly bible and read the song of Solomon (mehaliy mehaliy ze solomon). all 8 chapters tell us about the pride and groom saying 13 ፤ ውዴ ለእኔ በጡቶቼ መካከል እንደሚያርፍ እንደ ተቋጠረ ከርቤ ነው።
    14 ፤ ውዴ ለእኔ በዓይንጋዲ ወይን ቦታ እንዳለ እንደ አበባ እቅፍ ነው።
    15 ፤ ወዳጄ ሆይ፥ እነሆ፥ ውብ ነሽ፤ እነሆ፥ አንቺ ውብ ነሽ፤ ዓይኖችሽም እንደ ርግቦች ናቸው።
    16 ፤ ውዴ ሆይ፥ እነሆ፥ አንተ ውብ ነህ፥ መልከ መልካምም ነህ፤ አልጋችንም ለምለም ነው።
    17 ፤ የቤታችን ሰረገላ የዝግባ ዛፍ ነው፥ የጣሪያችንም ማዋቀሪያ የጥድ ዛፍ ነው።9 ፤ እኅቴ ሙሽራ ሆይ፥ ልቤን በደስታ አሳበድሽው፤ አንድ ጊዜ በዓይኖችሽ፥ ከአንገትሽ ድሪ በአንዱ ልቤን በደስታ አሳበድሽው።

  • በቻልኩት እግዚአብሔር በረዳኝ መጠን ለማንበብ እና ለመረዳት ሞክሪያለሁ ዕረፍትም ሰጥቶኛል።
    “የእኔ መሻትና ጥልቅ ፍላጎት እግዚአብሔርን ማክበር ነው። ይህንም እርሱ በወደደው መልኩ፣ በሰጠኝ ስጦታና አቅም ሁሉ ላደርግ እወድዳለሁ። ስለ ዘፈን እየሞገቱ መኖር የሕይወቴ ዐላማ አይደለም፤ ዘፈን መዝፈን የሚቻልበትና የማይቻልበት ሁኔታና አግባብ ቢኖርም ባይኖርም፣ ከዚህ በኋላ የእኔ ጕዳይ አይደለም። የምፈልገው እግዚአብሔርን በሁለንተናዬ ማምለክ ነው። የጌታ የሆኑትም ሁሉ የጊዜውን መክፋት እያዩ፣ ሰዎችን ሁሉ የሚወድደውንና አንድ ልጁን የሰጠውን እግዚአብሔርን በማወቅ፣ ካለውና ከሚመጣው ክፉ እንዲያመልጡ ነው። እነዚህም በነገር ሁሉ ኢየሱስ ክርስቶስን በመግለጥ ቢተጉ በዚህ እግዚአብሔር እንደሚከብር አምናለሁ።”
    ይህን አቋም የሚያፀና ፀጋ ይብዛልሽ።

    ልጠይቅሽ የፈለኩት
    አሁን በምድር ላይ ስለምታሳልፊው እና ስለምታምኚው ስለ የህብረት አቋምሽ ብሰማ ምን ታስብያለሽ?😍

  • Very interesting article, holy-write in my opinion, Thanks for sharing Zeritu, Am sure many including me will have life changing answers in this article, Hope we get to read more articles from Zeritu, maybe a book.

  • I wish የመጀመሪያውን የአማርኛ መፅሀፍ ቅዱስ ብታገኚውና ከላይ የጠቀስሻቸውን ጥቅሶች ከዛ ላይ ቢሆኑ

    • እህታችን፣

      ጊዜ ወስደሽ፣ አስበሽ፣ ያስተምራል ብለሽ የዘመናችን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ምዕመራን አንገብጋቢ ጥያቄ እየሆነ በመጣው ጉዳይ ላይ ሀሳብን በሚገባ በማብራራት ስለማጋራትሽ አመሰግናለሁ። ጌታ ይባርክሽ ልልም ወዳለሁ።
      መረዳትሽን እንዳጋራሽን (እንዳንቺ ያለ መረዳት ያላቸው ሌሎችም እንደሚያምኑት)፣ ዘፈን ወይም “ሙዚቃቂ ጥበብን” ከመንፈሳዊ ከባቢ ውጭ ሆኖ በእርሱ ለማገልገል መሞከር እንዳልሽው የተለየና ግልጽ ጥሪን ከጌታ የተቀበሉ ካልሆነ በስተቀር፣ ፈረንጆቹ እንደሚሉት ስሊፐሪ ስሎፕ ሆኖ በቀላሉ ከመንፈሳዊ ህይወት ሰዎችን ሊንሸራተት ይችላል። በማብራሪያሽ እንደጻፍሽው፣ ጌታን በማይከተሉ ሰዎች መካከል በዘፈን የማገልገል ዕድሉም ጠባብ ነው። እነዚሁ ለዚህ ዓላማ እንደተጠሩ የሚያምኑ ዘፋኞችና ሙዚቀኞች፣ ያን ጥበቃ ሊያደርግላቸው የሚችለውን የአገልግሎት ከባቢ ራሳቸው ለመፍጠር ጥረት ካላደረጉ በስተቀር፣ ከመንፈሳዊ ከባቢ ውጭ ያለው ሁኔታ አደገኛ ይመስለኛል።
      ቢያንስ በማብራርያሽ ሚዛናዊ አቋም እንዳለሽ አስተውያለሁ። እንደ ጌታ ደቀ መዝሙር ከደረስሽበት መንፈሳዊ መረዳት በመነሳት ነገሮችን በልዩ ጥንቃቄ እንደምትፈጽሚያቸውም ተረድቻለሁ። ሌሎችም በደፈናው ኃጢአት የለበትም በሚል፣ ኀጢአት በሆነውና ባልሆነው የዘፈን አቀራረብ መካከል በአገባቡ እንዲለዩ መምከሽ ትክክል ነው። መሥመሯም ቀጭን ስለምትመስለኝ፣ ሰዎች ሳያውቁ የዓለም መንደር ውስጥ ራሳቸውን ሊያገኙ ይችላሉ።
      ከምንም በላይ ግን መዝሙር ያልነውም ሆነ ዘፈን ያልነው ሙዚቃዊ ጥበብ ለነፍስ እጅግ ቅርብ የሆነ ጉዳይ ከመሆኑ የተነሳ “ዙሪያችንን ይዞራል” የተባለለት ጠላታችን ዲያብሎስ በዚያ በኩል በቀላሉ በወጥመዱ እንዳያጠምደን ልዩ ጥንቃቄ የሚፈልግ ጉዳይ ነው።
      በአጠቃላይ ግን፣ ይህ የዘፈን ጉዳይ አሁንም ተጨማሪ ውይይትና የተለያዩ ዕይታዎችን በዚህ መልኩ ማጋራት የሚፈልግ ስለሚመስለኝ ሌሎችም የሚሰማቸውን ወይም የተረዱትን እንዳንቺው ማቅረብ ቢችሉ አማኞችም ተገቢ የሆነውን መጽሐፍ ቅዱሳዊ ዕይታ እየያዙ ይሄዳሉ ብዬ አምናለሁ።

      ስለሁሉም ጌታ ይባርክሽ። ጸጋውም ይብዛልሽ!

  • የዘሪቱን አነብብኩት

    ጹሁፍ ዕውነቶች ቢኖሩትም ጥያቄ የሚያስነሱ ሃሳቦች አሉት::
    1 ስለ ዘፈን በአወንታዊ ተጠቅሶአል ብላ የጠቀሰችው ጥቅሶች ከብሉይ እና ከአዲስ ኪዳን ዘፈን የሚለው dance ወይም እንቅስቃሴውን እንጂ መልእክቱ ምን እንደሆነ አልተገለጸም
    2 እርሶ በምትለው መንገድ የትና እንዴት ማቅረብ ይቻላል:: ወደ ጌታ ያልመጣው ማህበርሰብ ይህ የተቀደሰ ነው ብሎ የሚቀበለው አይነት የሚሆነው በምን መልኩ ነው::
    3 ሌሎችን ለመድረስ ስለ ሃገር ስለ ተቃራኒ ጾታ ፍቅር የሚያዘሜ ስው እንዴት ብሎ ነው በሙዜቃው ሌሎቹን የሚደርሰው ? ጌታንስ እንዴት ሊያከብር ይችላል ?
    ምታደርጉትን ሁሉ ለጌታ ክብር አድርጉት ስለሚል ነው
    4 አለማዊ እና እርሶ ምትለው አይነት ሙዚቃ መለያው ቦርደሩ ግልጽ ባልሆነበት ሁኔታ ወጣቶችን ወደእዚህ መምራት በቤቱ ያሉትን ለማስወጣትና ለማሰናከል ምክንያት አይሆንም ወይ ?
    5 ዘሪቱ ወንጌላውያንን ግብዝ ለማለት ዳድቶታል :: በየትኛውም ዘመን ቤተክርስትያን ንጹህ እንከን አልባ ሆና አታቅም :: ችግር የሉብንም ማለት ሳይሆን ከድካማችን ተጨማሪ ሌላ የሚያደክም ሃሳብ ይዛ መምጣቶ አጠያያቂ ነው::
    መፍትሔው
    “”””””””””””
    እርሶ የምትለው ሙዚቃ በዘማሪዎች በወንጌላውያን ውስጥ አሉ::
    ለምሳሌ ስለ ትዳር ውስጥ ስላለው ፍቅር ገዛህኝ ሙሴ
    ስለ ሰርግ ጌታ ያውቃል
    ስለ ልጆች ገዛህኝ ሙሴ
    ስለሃገር ብዙ መዘምራን
    ውጭ ሳንወጣ በቤቱ ማድረግ ስንችል ለምን ጌታን በማያከብር መንገድ እናደርጋለን::

    በአጠቃላይ እዚህ መጽሔት ላይ ይህ መቅረቡ መጽሄት አዘጋጁ ይህንን ሃሳብ ተቀብሎታል ማለት ነው :: ይህ ደግሞ አደገኛ ነው::

    • 1፡ “በአጠቃላይ እዚህ መጽሔት ላይ ይህ መቅረቡ መጽሄት አዘጋጁ ይህንን ሃሳብ ተቀብሎታል ማለት ነው :: ይህ ደግሞ አደገኛ ነው::” ያልከው ትክክል አይደለም፤ ሰዎች የተለያየ ሃሳብን አንስተው ቢወያዩ ችግር አለው ብዬ አላምንም።

      2፡ ሙዚቀኛው ከ ቤ/ክ ውጪ እንደማንኛውም ባለሙያ (ተዋናይ፣ ገጣሚ፣ ደራሲ፣ ሃኪም…) ጥበቡን ማሳየት ቢፈልግ እና በሱም መተዳደሪያውን ቢከተል ለምን ይከለከላል ነው ዋናው ጉዳይ። ዘሪቱም እንደገለጸችው፣ እየሱስ ባለበት የሙዚቃ ባለሙያዎች ጥበባቸውን ሲያቀርቡ ከነበረ እና እሱም ሲቃወም (ቤተመቅደስ ወስጥ እንዴት በሃይል እንደተቆጣ በደንብ እናውቃለን) ካላየነው እና የሚያቀርቡት ነገር ሰዎችን የሚያቀና ከሆነ በእኛ ዘመን ለምን እንከለክላለን?

      • የትኛውን መጽሐፍ ቅዱስ እንደምታነቡ አላወኩም። ክፍሉን ግለጹ

      • ለምን ላይ ላዩን እናያለን? ዘሪቱ ስለዘፈን ያላት አመለካከት በብዙሃኑ ዘንድ ዘፈን ካለው ብያኔ ጋር የሚጣረስ ነው፡፡ ይህ እሷ ጋ ያለው ምልከታ ለእሷም በሚገባው ልክ የገባትም አይመስለኝም፡፡ ለምሳሌ በዚህ ፅሁፏ ያቀረበችው ጥንቃቄን የገደፈ ነገር አድርጋ ታውቃለች፡፡ ለምሳሌ አንድ ኮንሰርት ላይ ለብሳው የነበረ ልብስ ሞደስት ሳይሆን ልቅ ነበር፡፡ ያን አለባበሷን እዴት አድርጋ በእግዚአብሔር ቃል ትክክል መሆኑን ማስረዳት እንደምትችል አላውቅም፡፡ ከዚህ የምንረዳው ነገር የእሷ ምልከታ ከobjectivity ይልቅ subjectivity ስለሚያጠቃው በውጤቱ ለብዙዎች በሃጢአት መወስወስና መጥፋት ምክንያት ይሆናል፡፡ እንዴት ካላችሁኝ ለምሳሌ አንድ ሰው እሷ ካየችበት እይታ ወጣ ባለ መልኩ ከዘፈን ጋር ሌሎች ዘና የሚያደርጉ ነገሮችንም መጠቀም ምንም ችግር የለውም ምክንያቱም በምድር ስላለ ደስታ ስናወራ ስጋን ማስደሰት እስከሆነ ድረስ ስጋዬን ባስደስት ለምን ሃጢአት ይሆናል ቢል ስህተት ነው የምንልበት መለኪያ ምንድነው? መለኪያውንስ ማነው የሚያወጣው? ብቻ ከባድ ነው፡፡
        https://images.app.goo.gl/3L1GmAFNrvUU9nzo8

    • ደኅና መጥተህ መጨረሻውን አበላሸኸው። የመጽሔቱ አዘጋጅ የእኅታችን ዘሪቱን አሳብ ተቀብሎታል የሚለውን ከየት አመጣኸው? በዚህ ላይ “አደገኛ” በሚል ቃል አጦዝከው። መጽሔቱ ስለ ክርስትና እና በክርስትና ዙሪያ አሳቦች ተነበው እንዲንሸራሸሩና መጣጥፎች ማቅረቡ በጣም ያስመሰግነዋል። ይህ ማለት ግን የሚስማማበትን ብቻ ይለጥፍልናል ማለት ኣይደለም።

      በግሌ ይህ ጽሑፍ ጥሩ ነው ከሚሉት ነኝ። እንኳን መጽሔቱ ላይ መውጣቱ ቀርቶ፣ ጽሑፉ ራሱ አደገኛነ ተብሎ መፈረጁ ምንም ኣልስማማም።

    • 1. የሷም ሀሳብ ይኸው ነው፤ በደፈናው እንደተለመደው “ዘፈን” የሚለውን ቃል የእግዚያብሔርን ስም explicitly ከሚጠሩ ሙዚቃዎች ውጪ ያሉትን ሁሉ ከምንፈርድበት የሙዚቃው መልዕክት እግዚአብሔርን ያከብራል ወይም የመንፈስ ፍሬ (ገላትያ 5 ፥ 22-23) ነው ብለን እንጠይቅ ነው ያላቸው።
      2. ከላይ እንደጠቀስኩት ከመንፈስ ቅዱስ አንፃር የግጥሙን መልዕክቱን በመፈተሸ
      3. ቃሉ በግልፅ እንደሚለው :: “እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውም ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት።” (1ኛ ቆሮ 10፥31) የምንበላው የሚያስደስተው ምግቡ እግዚአብሔር የማይጠላው ሲሆን እንደሆነ ሙዚቃም ፈቃዱን ከምናውቅበት ከቃሉ አንፃር ፈትነን እንደ ቃሉ የሆነውን በማድመጥ / በመስራት ::
      4. በግሌ ይሆናል ብዬ አላስብም :: አማኙ ከመፅሀፍ ቅዱስ አንፃር ሙዚቃን መለየት ይችላል። ይህ ግን ለሙዚቃ ብቻ ሳይሆን ለሁሉም የጥበብ አይነቶች ነው ::

    • አንተ ያነሳኸው ጥያቄ ራሱ ጥያቄ ያስነሳል።
      ጥያቄዬ ምን መሰለህ “…ቤተክርስቲያን ውስጥ ማድረግ እየተቻለ ጌታን በማያከብር መንገድ ለምን ይደረጋል?” ላልከው
      ጌታን የማያከብረው በውጪ ስለሆነ ስለተደረገ ነው?? ወይስ ከመፅሀፍ ቅዱስ ጋር ከተጣረሰ?

  • በዋናነት ለሚለውጠውና ለሚመራው የእግዚአብሔር ቃል ያለሽን ረሀብና ለማርካትም ባደረግሽው የግል ጥረት የዘላለሙን ፈቃድ ስላገኘሽበት ሂደት አደንቃለሁ፤ ጌታዬንም በጣም አመሰግናለሁ። በተጨማሪም በመሰል ጥያቄና ሁኔታዎች ውስጥ ላሉት በደረሽበት መልስ ይሆናል ያልሽውን ሀሳብ ስላካፈልሽን ማመስገን እፈልጋለሁ በርቺ

  • I’ve found it very thoughtful one! I admire your honesty; in fact your life is in a better shape than those who condemn you.

    That being said, my reflection on the article is as the following:

    Let’s say that all the points – including the theological arguments- that have been mentioned in the article are correct. I believe that we will create a lots of room for “temptation” which could ultimately lead for committing sin. You have even tried to point out some defense mechanisms for a musician’s who would like to pursue this carrier. Isn’t it better to follow “avoidance” strategy ?

    Apart from this, I would like to extend my deepest gratitude and respect for you. God bless you more ; you are enlightened and smart women!

  • Interesting read and what I always wondered to myself … in my teenage years I used to ask why it is okay to write a love letter or a poem but not sing a love song.

    • የዕውነት እግዚአብሔር አምላክን ስለአንቺ አመሰግናለሁ፨ የእውነቴን ነው የግብዝነት አይደለም፨ ይህች አጭር መጣጥፍ እግዚአብሄር እንዴት አድርጎ በድብቅ እያሳደገሽ እንደሆነ ግልፅ ማሳያ ሆኖኛል፨ በርቺ!!! እንዳልሽው እግዚአብሄር ሲለውጥና ሲቀባ የትኛውን ግለሰብ ወይም ተቋም ማረጋገጫ አይፈልግም፨ ከዚህ ፅሁፍ እንደተረዳሁት በቀጣይ ለምድራችን ግልፅ የሆነ የክርስቶስ ደብዳቤ እንደምትሆኚ ነው፨
      በርግጥም በክርስቶስ የተከፈለልን ዋጋ፤ የዳነንበት ዕውነት በትክክል ስገባን ማናቸውም የምናደርጋቸውን ነገሮች የምንመዝነው ምግባራችን ውዳችንን ንጉሱን ኢየሱስን ያከብራል ወይ? በሚለው እንጂ ኃጢዓት ነው አይደለም? በሚል የማይመጥን ምክንያት አይሆንም፨ እንድናደርጋቸው የተፈቀዱልን ነገሮች እንኳን ሌሎችን የሚያሰናክል ከሆነ በመተው ኢየሱስን ማክበርና ማስከበር ላይ የተመሰረ እውነተኛ የክርስቶስ ህይወት መኖር ነውና የክርስትና ማዕከሉ!!!!

  • Lezebi yale tsufi, beradi woyim tikus mehoni new miyasifaligehu , revelation 3,15
    There’s no way huletun wodo endet medan yichelali …choose is on your hand tiwilidin gin
    Meberezin bitakomi yeteshele yihonal because double 🔥 frid endayi honibish .

  • I read each and every word with so much attention and amazement, i can see that you studied on this aspect well. It was an insightful article and I want to appreciate your value for the word of God in defining anything in life including this issue; Thank you for expounding on this topic. I believe we will serve this mighty God together in the days to come. You are a blessing!

  • ዘፈን አዳምጣለሁ በተለይም በ1970 ዎቹ መጨረሻና 1980ዎቹ ውስጥ የተዜሙትን ዘፈኖች።በነዚህ ጊዜያት ተማሪ ነበርኩ።አሁን የዚያን ጊዜ ዘፈኖች በአጋጣሚም ስሰማ የትምህርት ቤት ጓደኞቼን፥መምህራኖቼን(ከአንደኛ ደረጃ እስከ ስድስት ኪሎ/AAU) ፥ጋራ ሸንተረሩን (ቤታችን ከከተማ ወጣ ያለ ነበርና)…ያንን ወቅትና ክስተቶችን አስታውሳለሁ።
    በተለይም አካባቢያችን የምንጭ ውኃ ስለነበር ወሃውን ለመቅዳት ስንሄድ የአብተው ከበደን
    ዘፈን እንዘፍን ስለነበር አሁን ዘፈኑን ባጋጣሚ ስሰማው በሀሳቤ እዚያ የምንጭ ውሃውንና አካባቢው የነበረው ልምላሜ ውስጥ ይዞኝ ይጓዛል።ታዲያ ሃጢያትነቱ እምኑ ጋ ነው ?!
    ብዙሃኑ በችግር እየተጠበሰ በምቾት የሚንደላቀቀው/የሚሰክረው አገልጋይ ወይንም ነቃፊ የቤተክርስትያን ሽማግሌ ተብዬ ምን ሊባል ነው ?
    ለማንኛውም ዘርዬ ፈጣሪ የማየትና የመግለጽ አቅም ስለሰጠሽ ከልማዳዊ እምነት ነጻ ታወጪናለሽ!!

  • ጥልቅ የሆነ ፅሁፍ ነው ያቀረብሽው እግዚአብሔር በፀጋው ያኑርሽ።

  • Thank you for this piece. You should write more on other topics as well its incredibly sharp and thorough. Bless you sis.

  • Galatians 5:19-26
    King James Version
    19 Now the works of the flesh are manifest, which are these; Adultery, fornication, uncleanness, lasciviousness,

    20 Idolatry, witchcraft, hatred, variance, emulations, wrath, strife, seditions, heresies,

    21 Envyings, murders, drunkenness, revellings, and such like: of the which I tell you before, as I have also told you in time past, that they which do such things shall not inherit the kingdom of God.
    on number 21 revelling in amharic መረን የለቀቀ ፈንጠዝያ እንጂ ዘፋኝ አይልም።

  • የምታቀርቢውን ሃሳብ በቅዱሳት መጽሐፍት እውነት ለመደገፍ መሞከርሽ ጥልቀት የጎደለውና መልስ ከመስጠት ይልቅ በጥያቄ የሚሞላ ቢሆንም መልካም ነው እላለሁ። ነገር ግን የእውነት ለእግዚአብሔር ፈቃድና ደስታ የምትጨነቂ ከሆነ ይህንን ያክል ስለ ዘፈን ከመሞገትና የወንጌላውያኑን እሴት ቁልቁል ከመመልከት በመቆጠብ ግብዝ ባልሺያት ቤተከርስቲያን ጥላ ቢታድሪ አስተማሪ ይሆናል።
    ደግሞ አለማዊዉ ልምምድ እግዚአብሔር መሰልነትን ከትውልዱ ሕይወት እንደ መዥገር በሚመጥበት በዚህ ዘመን እንዳንቺ ብዙ ተከታይ ያላቸው ሰዎች ስለ ዘፈን ይህንን ያክል ጥብቅና ከሚቆሙ ሁሉን እርግፍ አድረገው በመተው ወደ ቃሉ እውነትና ወደ ቤተክርስቲያን ሕብረት ቢመለሱ በእጅጉ አስተማሪ ሊሆን ይችላል።

  • “ከእግዚአብሔር ዐሳብ በተቃራኒ ያሉ ብዙ ዓለማዊ ዕሴቶችንና አመለካከቶችን ዜማ ስለሌላቸው ብቻ እቅፍ ድግፍ አድርጎ የያዘ ማኅበረ ሰብ፣ በቅዱስ ቃሉ ላይ ግልጽ የሆነ ሙሉ ኵነኔ የሌለበትን የሙዚቃ ጕዳይ እንደ ጽድቅ መመዘኛ አድርጎ መውሰዱ ተገቢ ያልሆነ ብቻ ሳይሆን፣ ፍትሕ የጎደለው ሆኖ ይሰማኛል፤ በዚህም ፍርደ ገምድልነት ብዙዎች እንደተጎዱ አውቃለሁ።”

    ተደንቄአለሁ! 😍 ድንቅ ጽሑፍ ነው!

  • Ohh zeritu ,,,,መረዳትሽ እጅግ ጥልቅ ነው።የኛ ጌታ (selfless Christ) ድንበር የለውም ,,,,እና የት?እንዴት? እንደሚያገኝሽ አይታወቅም እናም ያስገርማል!

  • እጅግ የተወደደ መልእክት ነው።

    ጌታ ኢየሱስን የሚታስደስች ሴት ሆነሽ ቅሪ።

  • Wow! Such a courageous woman of God(a role model) who stands the ground of truth over mere people pleasing and acceptance. May God keep blessing you and shine him self through you. He is not a God of confirmation or mere uniformity and rituals but of truth and love, thanks for your fear less service in such a generation where services are bounded by majority pleasing.
    The institutional church couldn’t even do what your doing Zeritu, thanks for doing this as a part of the real body of christ.

  • I DO AGREE ON SOME POINTS BUT THERE IS NO LOVE MORE THAN JESUS CHRIST

    IF YOU LOOK AT OUR MANY ETHIOPIAN TRADITIONAL DANCE STYLE COMES FROM WORSHIP OF THE SPIRITS OF DARKNESS AS OTHER COUNTRIES.
    MOST IMPORTANTLY SECULAR MUSIC OR TRADITIONAL MUSIC ARE ALL WORSHIPING THE HUMAN BEING OR THE SPIRIT DIRECTLY OR INDIRECTLY

  • I agree music is not a sin at all, fallen human makes it. um gonna suggest u some verses and later end up by questioning
    First we believe art is generally God’s gift especially music or it’s biblical not just our belief.
    GOD commandes us to sing, ryt.
    second; “Therefore, whether you eat or drink, or whatever you do, do all to the glory of God” (1 Corinthians 10:31). we are also to do whatever is pure ,holy, good ….and so on.BUT i believe in the principle ” christian’s life should be vertical and horizontal”. as a christian we have a clear consciousness about anything ” the profit of believers and the salvation of unbelievers” so whatever we do, we can do it for the glory of GOD and the benefit of others. we can conclude to avoid distinction between secular and non secular because we are in secular world but still we r living there by avoiding evil things.
    but what about these verse

    13 Therefore let us stop passing judgment on one another. Instead, make up your mind not to put any stumbling block or obstacle in the way of a brother or sister. 14 I am convinced, being fully persuaded in the Lord Jesus, that nothing is unclean in itself. But if anyone regards something as unclean, then for that person it is unclean. 15 If your brother or sister is distressed because of what you eat, you are no longer acting in love. Do not by your eating destroy someone for whom Christ died. 16 Therefore do not let what you know is good be spoken of as evil. 17 For the kingdom of God is not a matter of eating and drinking, but of righteousness, peace and joy in the Holy Spirit, 18 because anyone who serves Christ in this way is pleasing to God and receives human approval. roman 14.”THE WEAK AND STRONG” verse. this concerns us, christians.

  • Johnson Mark I believe that Satan knows more about songs, its power and influence than any human being. He is therefore using secular music in a cunning and subtle way to lead many hearts away from God thereby plunging them into destruction.

    In Matt. 14, John the Baptist was beheaded after a dance put up by Herodias daughter. What type of music do you think was being played? Do you think this thing would have happened if they were praising or singing spiritual songs unto God? At the party, the songs, dances and fun had nothing about God (love, mercy, forgiveness, humility) but rather pushed Herod to display his wealth and power as a king. Matt. 14:1-12. In 1 Samuel 16, David plays his harp “ And it came to pass, when the evil spirit from God was upon Saul that David took the harp, and played with his hand: so Saul was refreshed, and was well and the evil spirit departed from him. Vs 23. The music made by David was filled with God’s anointing and power. It refreshed the soul and spirit of Saul, healed him and drove away the evil spirit which haunted him.
    It is true that some secular songs “may be educative”, however, everything one needs through music can be obtained through gospel songs, Christian literatures and most importantly God’s word. Secularism, which often comes from the word secular, in philosophy and politics means rejection of religious and sacred forms and practices in favor of rational assessment , decision-making and civil institutions of government. Hence a song can be considered as a secular if it does not regard God and the Lordship of Jesus Christ .

    • I see what your points are, I agree with most of them as well. However, the author’s theme wasn’t about doing music or encouraging people to pursue it. She has been rejected and condemned by many denominations leaders because of who she WAS once. As people who live on this earth, we all have flaws and commit sins in our day to day life and some times even in church. Most of us including the evangelical leaders despise what others do not in the way that correct them, rather they use it as a paint to hide their own ungodliness. Zeritu is one few people that I looked up to, her life is clear. She put the glory of God before her personal benefits, regardless how many times many evangelical leaders tried to disbarment her from following Jesus, she showed her perseverance and resilience to stand firm and gave up everything for Jesus. May God bless her. If I understand her article, the main point is to address how hard she is being taunted by her past not accepted for her willingness to change. As church family, we should be happier and encourage people for what way they want follow rather than which way they are coming from.

      God bless!

  • well articulated but still needs further thought and discussion. I admire you for coming to the front and bring this issue for learning and discussion.

  • ዘርዬ ፍቅርና ጥበብ ለሰጠሽ ጌታ ተገዝተሽ መኖርሽ ሁሌም አንቺን ሳስብ ውስጤ በመንፈሳዊው ቅናት ይሞላል። ጌታ ይባርክሽ

  • How i love the place you have for the word of God . It was very nice Zeritu as usual .. and the reasoning are all from the scripture. The so called even Gospel singers ain’t be such a Bold voice of Christ like you what can I say ..የሰላም አምላክ ራሱ ሁለንተናሽን ይቀድስ፤ መንፈስሽ፣ ነፍስሽ ሥጋሽ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚመጣበት ጊዜ ያለ ነቀፋ ይጠበቁ። የጠራሽ የታመነ ነው፤ እርሱም ያደርገዋል።

  • ጽሑፍሽ በእውነት ብስለትሽን (ክርስቶስን የመረዳትሽን ጥልቀት) ያየሁበትና በመጽሐፍ ቅዱሳዊ መረዳት የተቃኘ እይታ ላላቸው ፣ በስሜታዊነት ለመፍረድ ለማይቸኩሉ ፣ ቁንፅል ሀሳብ ይዘው ለማይሮጡና ማመዛዘን ለምችሉ ብስል ክርስቲያኖች የሚመጥን ጽሑፍ ነው ። ስለደረስሽበት የመረዳት ደረጃ ስለ አንቺ ጌታን አመሰግናለሁ❣️
    “በበሰሉት መካከል ግን ጥበብን እንናገራለን፥ ነገር ግን የዚችን ዓለም ጥበብ አይደለም የሚሻሩትንም የዚችን ዓለም ገዦች ጥበብ አይደለም፤” — 1ኛ ቆሮ 2፥6

    ይህንን ስል ግን የጻሺሽው ሁሉ ትክክል ነው እያልኩኝ አይደለም ። እንከን የለለው ፍጹማዊ ጽሑፍ የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ነውና

    ከጽሑፍሽ በጣም ደስ የሚሉ ነገሮች ፦
    ➊ #ለተጻፌው ለእግዚአብሔር ቃል ስልጣን ያለሽ መገዛትና ታላቅ አክብሮት ፤ ቃሉ ካለ የትኛውንም ነገር ለመተው በተዘጋጀ መንፈስ ሆነሽ ቃሉን እንደ ቤርያ ሰዎች ስታጠኝ በአይነህሊናችን የሚያስቃኝ ጽሑፍ ነው።

    ➋ የተጻፈውን የእግዚአብሔርን ቃል ከሀይማኖት ድርጅቶች ፣ ከባህልና ከሰዎች ይሉኝታ ጫና ውጪ ሆነሽ መጽሐፉ የሚለውን ለመረዳት መጣርሽ ሌላው ደስ የሚል ነገር ነው ።
    ➌ ሌላ ጽሑፍሽን ስታዘጋጅ ያደረገሽው #ታላቅ ጥንቃቄና ሚዛናዊነት እጅግ የሚደነቅ ቅኝትና አቀራረብ በመሆኑ በጣም ደስ ይላል ።

    ጽሑፍሽ ያየሁት አማካኝነት ያየሁት ድክመትሽ
    ለሙዚቃ ጥበብ ያለሽ ፍቅር ለጌታ ካለሽ ፍቅር ባይበልጥም በጽሑፍሽ ላይ ታላቅ ተጽእኖ ፈጥሯል ነገር ግን የጌታ ፍቅር አሸንፎ ታይቷል ። ከጽሑፍሽ የተረዳሁት ፦ አንቺ ከዘፈን አለም ስትወጪ ውድ ነገርሽን ሰብረሽ ውድ ሽቱሽን ነው ከጌታ እግር ያፈሰስሽው ።
    ይህ በጽሑፍሽ ውስጥ የተንጸባረቀው ለሙዚቃዊ ጥበብ ያለሽ ፍቅርና አድናቆት በአንቺ ውስጥ በእግዚአብሔር ቃል የተገራ በመሆኑ አንቺን ከጌታ ሊያርቅሽ ባይችልም እንደአንቺ ላልበሰሉ የሙዚቃ አፍቃሪያን መጥፊያቸው ልሆን ይችላል (ታዲያ የጻፍሽው እውነት ይቀበር? እኔ እንጃ)
    “የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።”
    — 2ኛ ቆሮ 13፥14

  • I guess it was only catholic church which doesn’t condemn decent musics. I was never thought in church that musics r sin but the music which leads to “adultery” are. I think the English word used for that specific version on Bible is “ogey” (I’m not sure if i spell it right!?)

  • Zerish you are deep as usual and you are real queen and I just accept the whole idea because of every thing is reasonable and what I have say is you are too real and GBU

  • What I love from this writing is this quote
    ”በሙዚቃዊ ጥበብ ሊገፉ ለሚወድዱ ሁሉ ማለት የምፈልገው፦ እንደ እግዚአብሔር ቃልና ፈቃድ ብታደርጉት የሚከለክላችሁ ሕግ የለም፤ ነገር ግን፣ ‘ማድረግ የምችለው የተሻለው ነገር ይህ ነው ወይ?’ ብላችሁ ከመጠየቅ ጀምሩ። ”
    “ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ሁሉ ግን የሚጠቅም አይደለም፤ ሁሉ ተፈቅዶልኛል፥ ነገር ግን ሁሉ የሚያንጽ አይደለም።”
    — 1ኛ ቆሮንቶስ 10፥23
    Thank you Zeritu!!

  • ….ለዘሪቱ ከበደ…..
    እኔ የዘሪቱ አካሄድ ብዙም አላማረኝም!

    እንደዚህ አይነቱ አካሄድ እጅግ በጣም አደገኛ ነው ምክንያቱም ደግሞ የወንጌልን እውነት በቅጡ ባልተረዳ ትውልድ መካከል እየኖርን እንደምንገኝ ማስተዋል ይኖርብናል
    ለዚህም ምክንያት ቤ/ክርስቲያን የፅድቅና የቅድስናን ትምህርት ማስተማር አቁማ ፣ በገንዘብ ፍቅር, በአለማዊ ግርግር እንዲሁም ፀጋ እና ነፃ ወጥተናል በሚል አውዱን ባልጠበቀ አስተምህሮ እና አውዱን ባልጠበቀ ጥቅስ ትውልዱ መረን እንዲወጣ ሆኗል, ንፁህ የሆነው የክርስቶስ ወንጌል ማለትም (ከዓለም ሀጥያት ነፃ የወጣንበትና የዘለዓለም ህይወትን ያገኘንበት የመዳናችንን ተስፋ) በህይወቱ እና በኑሮው የሚያስተምር በሌለበት, ያሉ የሚመስሉትም ቢሆኑ በፍሬአቸው ሳይሆን የሀይማኖትን ድምፅ ነው የሚያሰሙን…
    ዛሬ የእኛ የወንጌል አማኞች እምነታችን ወደ ሀይማኖት ስርአት ተለውጧል..
    እንደ ህብረት በጣም የሚያሳስበን በቁጥር እንዴት ከሌሎች እንደምንበልጥ ሲሆን በግለሰብ ደረጃ ደግሞ የሚያሳስበን እንዴት በስጋ ህይወታችን አለማዊ ጥቅሞችን እንደምናገኝ ነው የምናስበው

    ነገር ግን
    ስለ ቁጥር ብዛት አባቶቻችን በቁጥር እጅግ ጥቂት ሆነው በወንጌል እውነት በምድሪቱ ላይ ተፈርተው እና ተፅዕኖን ፈጥረው እንዲሁም የቅድስና ህይወት ማሳያ ሆነው አልፈዋል
    ስለ ግል የስጋዊ ጥቅሞችም ቢሆን ይህ የዓለማውያን ባህሪይ ነው, ክርስቶስን የምንፈልገው ለስጋዊ ጥቅሞቻችን ማስፈፀሚያ ከሆነ፣ እንኪያስ አህዛብ ጠንቋይ ቤት በመሄዳቸው አይኮነኑም

    ወንጌላችን ፅድቅ ነው, ቅድስና ነው እውነት ነው ፍትህ ነው, በምላስ ሳይሆን የወንጌሉን ፍሬዎች እያፈራን በህይወት እንድንኖር ነው የሚያስተምረን።

    የትኛው የቀደመ ሐዋርያ እና ደቀ መዝሙር ነው ህይወቱ አልጋ በአልጋ ሆኖለት ያለፈው ጳውሎስ ነው, ጴጥሮስ ነው, ፊሊጶስ ነው ወይስ እስጢፋኖስ…እያልኩ እጠይቃለሁ???
    ይልቁንስ እነዚህ ደቀ መዝሙሮች ስለ ወንጌል በሰይፍ ስለት ወደቁ እንጂ። ዛሬ ዛሬ ለእኛ የተለየ ፅድቅ, ነፃነት እና ፀጋ ከወዴት እንደመጣ አይገባኝም ወይስ የቀደሙት ሐዋርያት እና የጌታ ደቀ መዝሙሮች ተሳስተው ነበር, ወይስ የአዲስ ኪዳን ሰዎች አይደሉም, ወይስ መፅሐፍ ቅዱሱን ቀዳደን እንጣለው እና ይለይልን…እያልኩ እጠይቃለሁ???

    የዘመኑ ሀሰተኛ መምህራንማ መፅሐፉን ቀደው ቢጥሉና የዓለምን ኑፋቄ ትምህርታቸውን በነፃነት ግተው ባጠጡን ነበር ነገር ግን እኛ እንኳን አፋችንን ብንዘጋ ቅዱሱ መፅሐፍ እራሱ እየተዋጋ ጠላት ሆኖባቸዋል

    አንድ የማይለወጥ እና የማይገረሰስ እውነት!!!
    ፅድቅ ፅድቅ ነው ቅድስናም ቅድስና ነው አበቃ።
    ስሜት እና ፍልስፍና ግን እራሳቸውን ችለው ነው መቀመጥ ያለባቸው

    ከዚህም የተነሳ እህቴ ዘሪቱ
    የተናገርሽው ንግግር የግል ስሜትሽን ነው እንጂ እውነት አይደለም

    መፅሐፍ ቅዱሳችን በግልፅ ዘፈን ሀጥያት እንደሆነ ይነግረናል ያብቻ ሳይሆን ዘፋኝ መንግስተ ሰማይን አይወርስም ብሎ ይደመድመዋል ይህ የመረረ እውነት ነው። እየተለሳለሰ ወይም እርዕስ እየተመረጠለት የሚፀድቅ ዘፈን የለም የለም የለም። እህቴ ዘሪቱ እንኳን በዚህ ትውልድ መካከል የምንኖረው እኔ እና አንቺ ቀርተን, ጳውሎስና ጴጥሮስ እንኳን ሀሳብ ቀይረናል ብለው “ቅዱስ የሆነ ዘፈን አለ” ቢሉን እንኳን ተቀባይነት አይኖረውም! (አይሉንም እንጂ!)…ምክንያቱም የእ/ር ቃል እርስ በርሱ አይጋጭም

    እህቴ ዘሪቱ ደግሜ የምነግርሽ ነገር እኔ እና አንቺ መፅሐፍ ቅዱሱን አራሚና አዳሽ አይደለንም
    በመዝፈናቸው ምክንያት በህሊናቸው የሚወቀሱት ሁሉ እየተወቀሱ ይኑሩ ወቀሳውን መሸከም ያልቻሉት ደግሞ ወደሚወዳቸው አምላክ ይመለሱ ምክንያቱም ስለ ሀጥያታችን የሚወቅሰን የእ/ር መንፈስ ነውና
    ስለዚህም ከወቀሳቸው ነፃ ልታወጪያቸው አትሞክሪ እ/ርን ትቃወሚያለሽና

    ከላይ, ስለ አሁኗ ቤተ ክርስቲያን ሁኔታ በጥቂቱ ለመግለፅ እንደሞከርኩት ቤተ ክርስቲያኒቱ ትውልዱን በሚገባ በወንጌል እውነት ተከታትላ እያሳደገችው አይደለም ፣ አማኙ በተለይም ወጣቱ በቋፍ ነው ያለው የዓለም ዳንኪራ ውስጥ ለመግባት ትንሽ ሰበብ የሚፈልግ አማኝ ነው
    ስለዚህ እህቴ ዘሪቱ ያንቺ አይነቱ ንግግር ለዘፋኞቹ ብቻ ሳይሆን ለአማኙም ጠንቅ ነው ይህ ብቻ አይግረምሽ ላንቺም ለራስሽ አደገኛ ነው ምክንያቱም ወደኋላ ይጎትትሻል
    ሀጥያትን በስሙ ጠርተን እንፀየፈው አናለሳልሰው, አናለዝበው ካለበለዛ ቀስ በቀስ ድሩን አድርቶ ጠልፎ ይጥለናል

    በመጨረሻም፣
    ዘፈንን ከሌሎች የአርት (የኪነጥበብ) አይነቶች ጋር አዳብለሽ ስላስቀመጥሽበት ሁኔታ..
    አንድ ልንረዳ የሚገባን ነገር Song is a kind of worship እኛ በአማርኛው መዝሙር እና ዘፈን ብለን እንከፋፍለዋለን እንጂ, ጥያቄው ማንን ነው worship የምናደርገው???
    በዘፈን ዓለምን በመዝሙር ደግሞ እ/ርን
    በሙዚቃ እና በዜማ ውስጥ መንፈስ እንዳለ ያልተረዳ ሰው ሞኝ ነው, (እኔ እና አንቺ ግን ሚስጥሩን በደንብ እናውቀዋለን) ፍጥረት ሁሉ ሙዚቃን ሲያዳምጥ የሚካፈለው መንፈሳዊ ነገር በእርግጥ አለ ለዚህ ነው ሙዚቃ አልወድም የሚል ሰው እታገኚም (ወይ በመዝሙር መልክ ወይ በዘፈን መልክ ማለት ነው)

    ሰው ሙዚቃ ሲያዳምጥ ወይ ያለቅሳል, ወይ ይተክዛል, ወይ ይቆጣል, ወይ በደስታ ይፈነጫል…ብቻ አንድ የሆነ መንፈስ ያገኘዋል (እንደ ሙዚቃው መልዕክት ይወሰናል ማለት ነው)
    ሌሎቹን የአርት (የኪነጥበብ) አይነቶች ብንወስድ ግን ከስሜት የዘለለ ክፋት የላቸውም…ለምሳሌ፣ አንድ በጣም የምትወጂውን ሙዚቃ ለስንት ጊዜ ሰምተሽዋል? እና አንድ በጣም የምትወጂውን ድራማ ለስንት ጊዜ አይተሽዋል? መልሱ ግልፅ ነው በትንሹ እንኳን በአንዲት ቀን ብቻ ሙዚቃውን የምትሰሚበት ቁጥር እጅግ ብዙ ነው መስማት ብቻ አይደለም የሙዚቃ አደገኛነቱ ስናዳምጠው ለእያንዳንዱ መልዕክት በህይወታችን ትርጉም እየሰጠን ነው የምናዳምጠው

    እህቴ ዘሪቱ መፅሐፍ ሲናገር እልፍ አእላፍ መላዕክት በእ/ር ፊት ቅዱስ ቅዱስ እያሉ ያለማቋረጥ በዝማሬ እንደሚያመልኩት ነው የሚነግረን እንጂ መላእክት በእ/ር ፊት ልዩ ልዩ የኪነ ጥበብ ትዕይንቶችን ለምሳሌ (ድራማ ፣ ውዝዋዜ ፣ የግጥም ምሽት ፣ የስዕል ጉብኝት ፣ የፋሽን ሾው እና የኮሜዲያን) ስራዎች የሏቸውም።
    ያላቸው መዝሙር እና አምልኮ ብቻ። አየሽ ሙዚቃ መንፈሳዊ ነው የምልሽ ለዚህ ነው

    ሰይጣንም ለዚህ ነው አብዝቶ የሙዚቃውን ኢንዱስትሪ ለመቆጣጠር የሚተጋው…በዘፈን ውስጥ ብዙ አይነት እርኩሰት ይተላለፋል ለዚህም ዘፈንን አምርረን እንጠላዋለን ህይወታችንንም ከክፉ መርዙ በፀሎት እንጠብቃለን!

    አንዳንዶች ዛሬ ዛሬ ሆድ ሲብሳቸው, ሲያኮርፉም ወይም በዓለማውያን ኑሮ ሲቀኑ፣ የሚሏት ፈሊጥ አለች…እርሷም ከእ/ር ቤት ወጥቼ እሄዳለው, ከዛሬ ጀምሮ አታገኙኝም እያሉ ያስፈራሩናል አንዳንዶቹም እዘፍናለሁ እያሉ አስፈራርተውናል
    ይሄ ነው እንግዲ ክርስቶስ ፊደል እንጂ ህይወት ያልሆነው ትውልድ

    ስለዚህም ወገኖች መልዕክት ስናስተላልፍ በዙሪያችን ስላሉ ብዙ ነገሮች እያሰብን መሆን አለበት ለማለት እወዳለሁ

    የመዝሙር ፀሐፊ
    ዶ/ር. ልዑል ግርማ

  • ባቀረብሽው ጽሑፍ ላይ ሁለት ነገሮችን ማለት እፈልጋለሁ ።
    1) መደምደሚያሽን ገንቢ እና አስተማሪ ሆኖ ስላገኘሁት እቀበለዋለሁ።
    2) ሀሳብሽን ለማስረዳት subjectively የሄድሽበትን መንገድ በፍጹም መቀበል አልችልም። ለምሳሌ አንድ ቦታ ስለ ክርስቶስ ይሄን ሀሳብ አጋርተሻል
    “በተለያየ ጊዜ ከተለያዩ ወዳጆች ጋር ኢየሱስ በሠርግ ቤት ወይም በተመሳሳይ የባሕላዊ ጨዋታዎች ቦታ በሚገኝ ጊዜ የሚኖረው አኳኋን እንዴት ይመስላችኋል የሚለውን ጥያቄ እንጠይቃለን።”
    አንቺ የሚመስልሽን ወይ እኛ የሚመስለንን ሳይሆን actually የሆነው ነገር ምንድን ነው? ኢየሱስ እንዲህ አይነት ነገር ሲገጥመው ምንድን ነው ያደረገው? የሚለው ላይ ነው ትልቁ ጥያቄ ያለው። ለዚህ ደግሞ ቅዱስ ቃሉ ስለዚህ ሁኔታ ያሰቀመጠው ነገር ምንድነው? objectivly ብቻ ነው መነጋገር የሚቻለው።

  • በእህታችን ዘሪቱ የተፃፈውን ይህን ፅሑፍ ደስ እያለኝ አንብቤዋለሁ። በብዙ እዉነትና እዉቀት የተሞላ ከመሆኑ የተነሣ ከዘፈን ጋር ተያይዞ የነበረብኝን ብዥታ ያጠራ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። የመፅሐፍ ቅዱስ ምሁራንን ጨምሮ ከመፅሐፍ ቅዱስ እዉነት ይልቅ በልምድ የምንመራ አብዛኞቹ የዘመኑ አማኞችን የሚሞግት ነው። ለሙዚቀኛዉ የሚያስተላልፈው መልእክት ደግሞ ከሁሉም የላቀ ነው ብዬ አምናለሁ።

    የእግዚአብሔር ፀጋ ይብዛልሽ ዘሪቱዬ
    ቀጣይ ፅሑፍሽን በናፍቆት እንጠብቃለን

  • Yene wed ehet. Zefenun endmtwijiw geltse nw westesh yegba lifeshim nw. Getanm wedshwal geltse nw. Mezmur eychalesh mezfenu gn lene trgum aysetem. YE SEWOCH ADERA TEYIW ENA YE KIRSTOS ADERAN TEKBEYI. Lemastarak atsekayi. Ur very wrong! Geta bechawun ybekashal Legend musicians and agelgayochnm tetsh getan becha eyi.

  • እንደ አጠቃላይ ጥሩ ፅሁፍ ነው። ሀሳብሽን ለማስቀመጥ የሄድሽበት ርቀት የሚበረታታ ነው። ነገር ግን በአንዱ ንዑስ ስር “ኢየሱስ ቢሆን ምን ሊያደርግ ይችላል” በሚለው ሀሳብ ላይ የተቀመጠው analogy መፅሐፍ ቅዱስ የማይደግፈውና ምንም አይነት አመክንዪ የሌለው ነው። እንዲሁም “የኢየሱስም የሙዚቃም መሆን ይችላል” የሚለው አረፍተ ነገር እግዚአብሔር ወልድን ከሙዚቃ ጋር በተነፃፃሪነት የሚያስቀምጥ ስለሆነ በእጅጉ እርምት ያሻዋል ።

  • የበረደውን ስርዓት አልባ ንትርክ እና ስድብ መቀስቀስ ሊሆን ይችላል እንጂ ይህንን ጽሑፍ በቪድዮ መልክ ብታቀርቢው ሊደርሳቸው ለተገባቸው ለብዙዎች ይደርሳል ጠቃሚም ይሆናል። በተለይም ለሙዚቀኞች የሰጠሽው እናትነት የተሞላው ምክር መደመጥ ይኖርበታል። በጣም ነው የምወድሽ አንቺን ቀና ልብ ይዞ ያደመጠሽ ሁሉ ባይስማማ እንኳ ቅንነትሽን እና እውነተኛ ክርስቲያን መሆንሽን ይረዳል።

  • You don’t like when others criticize your children and focus on their faults and misdeeds.God is the same, He will educate and help His children to rectify faults and misdeeds.
    He will chastise us when we do wrong and wants us to mend our ways.He despises when others find faults in US and when WE find fault in each other.WHY???🙏❤️♥️🧎🇮🇱🕎😇✡️😇😇🇮🇱🙏✡️🧎♥️❤️❤️❤️

  • በእውንነቱ እውነታውን ያስቀመጥሽበት መንገድ አስደስቶኛል። ከእውነት ይልቅ ልማድን አቅፎ ለያዘውና በዚሁ ለመቆየት አይኑን ለጨፈነ ሁሉ አሪፍ ሙግት ብዬ አስባለሁ። ቀጣይ ጽሁፎችሽን በጉጉት እጠብቃለሁ። እግዚአብሄር ጸጋውን ያብዛልሽ!!

  • እህት ዘሪቱ እኔ ገና ድሮ ከአስራ አምስት አመት በፊት የክርስቶስ ተከታይ ነኝ ሳትይ በፊት እግዚአብሄር ታላላቅ የመዝሙር ኮንሰርቶች በማዘጋጀት እንደሚጠቀምብሽ እንዲሁ ይሰማኝ ነበር ኢየሱሥን መከተል ጀመርኩ ስትይ አልገረመኝም አመሰገንኩ እንጂ ገና ብዙ እንደሚጠቀምብሽ ይሰማኝ ነበርና ወደጥያቄ ግን ስገባ የሮሜ 14 ዋና ሀሳብ ክርስቶስ የሞተለትን ሰው ከማሰናከልም አንጻር ልክ ምንላቸው ነገሮችን ሁሉ በመተው መኖር በሳል ክርስቲያናዊ አካሄድ መሆኑንና በዚህም አስተሳሰብ መመላለስን እንዳለብን ያስገድደናል(ክርስቶስ የሞተለትን አታሰናክለው ይላልና)። መዝፈን ልክ ነው ምንልበት መስፈርት ቢያሸንፍም እንኳን ስለሌሎች ብለን ሀሳቡን መተው አይኖርብንም? ዘፈንን በርግጥ በምንኖርበት ማህበረሰብ ውስጥ ያለውን ምልከታ ያላጤነው አካሄድ ሰዎችን አያሰናክልም ትያለሽን ማህበረሱ ያንቺ አይነት አመለካከት ባልያዘበት ሁኔታ ማገልገልሽ ዋጋ ይኖረው ይሆንን ከማሰናከል በቀር? ዘፈን ከምንኖርበት ማህበረሰብ ባህል አኳያ ልክ መሆኑና አለመሆኑ አይወሰነም ትያለሽን? አንዱ ችግራችን የእስራኤላውያንን ባህልና የዘፈን ምልከታ ትርጉምም ጭምር ቀጥታ እኛ ጋር ማምጣታችንም ይመስለኛል ። ለምሳሌ ወንድ ጸጉር ማሳዳገ አለበት ወይም የለበትም ሚለውን ክርክር ሚፈታው ክርክሩን ሚያቀርቡት ሰዋች ባህላዊ ሁኔታ ታይቶ ነው ለምሳሌ ለእስራኤላውያን ጸጉር ማሳደግ ለእግዚአብሄር ራስን የመለየት ወይም ናዝራዊነት ምልክት ነው ለቆሮንቶስ አማኞች ግን ባህላቸው አይፈቅድላቸውም እነሱ ጋር ይህ ልምምድ የለምና ።ዘፈንንም ከዚህ ባህላዊ ሁኔታ cultural background አንጻር በኛ ሀገር ያለውን ባህላዊ ፍቺ መጠበቅ አለብን ባይ ነኝ ሌሎችን ላለማሰናከል ብለንም ጭምር።

  • Bible is all about christ weather secular music is allowed or not it doesn’t matter. Since our song or preaching is not about Jesus it is not spiritual period
    When we come to music …. as for me many so called gosple musics are not spritual. i couldn’t see any difference between teddy afro’s song “Ethiopia” and other gosple singers song about Ethiopia
    there fore sin is unbelief. But if we believe in Jesus we can’t lieve for this world we can’t sing glory of this dirty world.it is impossible for me to sing about miner issues after seeing the major and amazing grace of my lord Jesus
    How can i dance for romantic love ? How can i raise my hand up for the creatures?
    Cause the creater is in me his name is Jesus i’m in live with him
    he is worthy of my all admiration my song and my talent

  • የተጻፈው ነገር መሬት ላይ ያለ እውነት ነው ነው። ለአገልጋዮች እና ለመጽሐፍ ቅዱስ አስተማሪዎች ትልቅ የቤት ሥራ የሰጠ ጽሁፍ እንደሆነም አምናለሁ። ተድበስብሰው የታለፉ ሀሳቦች ለትውልድ ነቀርሳ (የሚባላ ጭንቁር) እየሆኑ ነውና በጊዜ ሳይረፍድ ትውልዳችንን እናንቃ እላለሁ። እኛ ካልነገርነው እና ካላስተማርነው በውጪ ሆነው ለትውልዱ ጥፋትን የሚያስተምሩ ብዙዎች አሉና።
    ይህንን ጉዳይ ከባድ የሚያደርጉ ነገሮች ናቸው ብዬ የማስባቸውን ልጥቀስ፣
    1. ግራጫው ክልል (gray zone) የሚባለው ነገር ይህንን ርዕሰ ጉዳይ የተወሳሰበ ያደርገዋል። እስከምን ድረስ ነው ዘፋኞቹ መዝፈን ያለባቸው? የትኛውን መስመር ቢያልፉ ነው ኃጢአት የሚሆነው?
    2. አማኝ ላልሆኑ ሰዎች መልዕክቱ ምንድነው? የሰውን ልጅ ውድቀት እና ኃጢአተኝነት፣ የእግዚአብሔርን ፍቅር እና የኢየሱስ ክርስቶስን የመስቀል ሥራ፣ ንስሐና ወደእግዚአብሔር መመለስን ማዕከላዊ መልዕክቱ ካላደረገ ይህ “ዘፈን” ከልማቱ ጉዳቱ አይበዛም? ማለትም አማኝ ያልሆኑ ሰዎች ከእነዚህ ነገሮች ውጪ የሆኑ ለሥነምግባር እና ግብረገብ ጥሩ የሆኑ ነገሮችን ብቻ ቢሰሙ “ዳግመኛ ካልተወለዱ” የዘላለም ፍርድ እና ሞት እንደሚጠብቃቸው እንዴት ሊረዱ ይችላሉ?
    3. አብዛኛው የሀገራችን “አማኝ” መጽሐፍ ቅዱስን አያውቅም። ይህም በአለም ላይ በቅርቡ በተደረጉ ጥናቶች በክርስቲያን ስም ከሚጠሩ አብያተ ክርስቲያናት አማኞች ውስጥ ቢያንስ አንድ ጊዜ መጽሐፍ ቅዱስን ያነበበ ከ3% በታች መሆኑ ተገልጿል። እና ይህን አማኝ እንዴት አድርገን ነው ለእንደዚህ አይነት “አጥንት” ለሆኑ ሀሳቦች ክፍት ማድረግ የምንችለው?

    ሰፋ ያሉ ሀሳቦች ይንሸራሸራሉ ብዬ አስባለሁ።

  • ❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤❤

  • ፊልጵስዩስ 3
    ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
    ¹³ ወንድሞች ሆይ፥ እኔ ገና እንዳልያዝሁት እቈጥራለሁ፤ ነገር ግን አንድ ነገር አደርጋለሁ፤ በኋላዬ ያለውን እየረሳሁ በፊቴ ያለውን ለመያዝ እዘረጋለሁ፥
    ¹⁴ በክርስቶስ ኢየሱስ ከፍ ከፍ ያለውን የእግዚአብሔርን መጥራት ዋጋ እንዳገኝ ምልክትን እፈጥናለሁ።

    ጥቅስ እየ ጠቀሱ ዘፈንን ወደ እግዚአብሔር ቤት በጥበብ መልክ ሊያስገቡ እየሞከሩ ያሉት ለዘርቱና ለመሰሎቿ ተጠንቀቁ !
    ለዘፈን ህግ የለም ትላሌች!
    ዘፈን ስራ ወይም ጥበብ መሆኑን ከእግዚአብሔር ቃል እስቲ አሳይን!
    ቅዱስ ዳዊት , ልጁ ሰለሞን ወይም ሙሴ , ኢሳያስ… ወይም ከሐዋርያቱ የዘፈነ ማነው ?
    ስለ እግዚአብሔር ፍጹም ሙላት የምታወሪ ከሆነ ! እግዚአብሔርን መምሰል የሚታወሪ ከሆነ በጸጋ ስጦታ ብቻ ማን ነው የደረሰው ?
    እግዚአብሔር ስለ ጸጋ ስጦታው አይጸጸትም ይላል ቅዱስ ቃሉ ስለዚህ
    ይህ ጸጋ ለሁሉም ሰዉ ነው 1ኛ ቆሮንቶስ 12:8-11
    ነገር ግን እግዚአብሔር ጸጋውን የሚሰጠው ለሰውየው ጥቅም ብር ማገኛው መንገድ , ባር ሳይሆን ወይም ስሜቱን እንድገልጥበት ሳይሆን እግዚአብሔር እራሱ በልጁ ኢየሱስ በኩል ክብርን ,ምስጋናን ,አምልኮን እንድቀበል ነው።
    ስለዚህ ይህ ስጦታ ለወንጌል አገልጋዮችንም ይጨምራል እየሰረቁ እየዋሹ በዝሙት መድረክ ላይ ቢቆሙም ጸጋው ይሰራባቸዋል ! እግዚአብሔር ስለ ጸጋ ስጦታው አይጸጸትም ።
    ሃዋርያው ጳውሎስ እኔ ግን የሚበልጠውን አሳያችኋለሁ እንዳለው እኔም እንድሁ እላሌው:-
    1 ጻጋ ስጦታ
    2 ቅባትና
    3 ክብር
    የጸጋ ስጦታ(ተስጦ) ለማንኛውም ሰው ስሆን, ኢየሱስን ላመኑት መንፈስ ቅዱሳን ለተቀበሉት ግን የመንፈስ ስጦታዎች አሉ 1ኛ ቆሮንቶስ 12:8-11
    2 ቅባት:- ብዙ አይኔት ቅባት ቢኖርም ቅባት የሚሰጠው ለተመረጠ ሰው ብቻ ነው! እግዚአብሔር ቅባቱን ስሰጠን ለተለየ አላማ ነው
     “እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤”
      — ሐዋርያት 10፥38
    ቅባት የተገለጠ የእግዚአብሔር ኃይል ነው. ቅባት የተቀበለው ሰው ይለያል ከአለም ከራሱ ከቤተሰቡ ለእግዚአብሔርና ለእርሱ ብቻ መኖር ይጀምራል ።
    ምናልባት እዚህ ጋር ማለት የሚፈልገው የዘርቱ መዝሙር የክርስትና የመገለጥ ጥግ ኢየሱስ ያድናል ቢለው መዘመር ልመስላት ይችላል!
    ግን በፍጹም አይደለም ኢየሱስ ያድናል ብለን መዘመራችን መስበካችን ግዴታችንንና ስራችን ነው !
    የክርስትና ጥጉ እኔ የአባትን ፊት ማየት ነው እላለሁ ! የአባትን ፊት እያዩ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ የሚለው ከመላእክትና ከቅዱሳን ጋር አብሮ መዘመር ነው ብየ አስባለሁ ! ያንን ህይወት እዚህ መኖር ነው እላለሁ።
    ይህ ለማድረግ ግን ፍጹምነት ይጠይቃል , የሰማይ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተም ፍጹማን ሁኑ ።
    የሚለው ምን ማለት እንደ ሆነ መረዳት ያስፈልጋል !

    3ኛ ክብር :- ክብር ማለት የእግዚአብሔር ክብደት ስሆን
    ክብር የእግዚአብሔር ማንነት በእና ላይ ልክ እንደ ሙሴ ከተራራው ስወርድ ልክ እንደ ኢየሱስ በተራራው ላይ…
     ማንም ሰው በራሱ ልንሸከመው አይችልም ሰውየው ሙሉ በሙሉ እግዚአብሔር ከልተቆጣጠረው በስተቀር !
    ስለ ክብር ብዙ አልልም በእኔ ስገለጥ ታያላችሁ።

     “እርሱንና የትንሣኤውን ኃይል እንዳውቅ፥ በመከራውም እንድካፈል፥ ወደ ሙታንም ትንሣኤ ልደርስ ቢሆንልኝ፥ በሞቱ እንድመስለው እመኛለሁ።”
      — ፊልጵስዩስ 3፥10-11

  • “ስለ ዘፈን”
    ሁሉን እርግፍ አድርገሽ፣ እንደ ንስር፣ በአዲስ ማንነት ውጪ፣ ተጠንቅቀሽም ብረሪ።
    ከጌታ ጋር እንደ ጥሩ ልጅ መኖርን ከሁሉ በፊት ተለማመጂ።
    “የሰው ልጅ ሊያገለግል ነፍሱንም ለብዙዎች ቤዛ ሊሰጥ እንጂ እንዲያገለግሉት አልመጣም…” የማቴዎስ ወንጌል – 20:28
    ብዙዎቻችን መንገዱ የራቀብን እዚህ ጋ ነው፤ ጥሩ አማኝ መሆን እንጂ ጥሩ ዘማሪ (ዘፋኝ) መሆን ቀላል ነው።

    ብሩክ ሁኚ ዘሪቱ !
    Teka

  • Wow Zeritu!! This is extra ordinary view & great that I totally agree with!! God bless you in all your way and please keep it up.

  • ስለ ዘፈን ለዘሪቱ ከበደ
    በዓለም እየተሳብኩ ስመጣ ዘፈን መውደድ ሲጀማምረኝ ለመጀመሪያ ግዜ ከቮይስ ሙዚቃ ቤት የገዛሁት የአንቺን ዘፈን ነበር ያኔ 17 አመቴ ነበረ ክርስቲያን እና የክርስቲያን ቤተሰብ ልጅ እንደመሆኔ ቤት ውስጥ በነበረው አንድ ቴፕ ተደብቄ እሰማሻለው ዕድሜዬ ሲጨምር የአለም ተፅህኖ በህኔ ላይ ሲበረታ አለማዊነቴ እና አለምን መውደዴ ገሀድ እየወጣ መጣ ያዳቆነ ሠይጣን እንደሚባለው አይነት ዘፈኖችሽን በመውደድ የተጀመረው አድማጭነቴ ወደ አክራሪ አድናቂነት የሐሳቦችሽ ተገዢ ጥግ የሌለው አድናቆት ተጠናወተኝ የዘፈንሽ ብቻ አይደለም የሐሳብሽ ታሳሪ አየሆንኩ መጣሁ በህኔ መጠን የሚያደንቅሽ ካለ እንጃ ዙሪያዬ ባሉ ሰዎች ቤተሰቦች ሁሉ በአንቺ ጉዳይ የታወቅሁ ነበርኩ ሽንጤን ይዤ ነበር ለዘፈንሽ እና ሐሳብሽ ምከራከር የነበረው እንዲህ እላለሁ ስገልፅሽ ዘሪቱ ሁሉ ነገር አላት ስታይሊሽ ናት ትደንሳለች ገጣሚ ናት ዜማ ታውቃለች ሐሳቧን መግለጥ አትፈራም ሙሉ ናት እላለሁ
    ያለፈው አልፎ አለምን ከመውደድ የተነሳ የህይወት ኪሳራ ውስጥ ገብቼ እያለሁ ኢየሱስ ከአለም ከጨለማ ከራሴ ዳግም በደሙ ዋጀኝ በምህረቱ ባለጠጋ ነውና በአዲሱ ሰውነት ውስጥ ለሁለት አመት ስኖር ጌታ በእግሮቼ ስር ካስረገጠኝ የአለም ከንቱ ነገሮች አንዱ ቀላል የሆነልኝ አጅግ የምወደው የገዛኝ የነበረውን ዘፈን ነው
    ጌታዬን ኢየሱስን በተቀበልኩ ብዙም ሳልጠነክር አስቀድሜ የምወደውን ዩትዩብ ላይ ከፋትሱ ጋር ያደረግሽውን ቃለመጠይቅ አየሁት ግን እንደበፊቱ አልወደድኩትም ትርጉምም አልሰጠኝም ራሴን እጠይቃለሁ ራሴን ለማፅደቅ እየሞከርኩ ነው ? ፅንፍ እየያዝኩ ነው ? ዘፋኝ የሆነችውን አስቀድሞ የምወዳትን ዘሪቱን ልጠላት እየሞከርኩ ነው ? እያልኩ ቃለመጠየቁን አየዋለሁ ፍፁም ትርጉም አልሠጠኝም እንደ ፍልስፍና የማየው አስቀድሞ የምመሰጥበት ከድፍረት ንግግሮችሽ አንዱ የሆነውን ኢየሱስ ሙዚቃ አይጠላም የሚለውን ወደ ልቤ ላቀርበው ብሞክርም አልሆነልኝም ቪዲዬውን እያየሁ ለምን አልተመሰጥኩበትም እንደቀድሞው ? እላለሁ ይህን እያሰብኩ በውስጤ ይህን ቃል ሰማሁት “በክርስቶስ ላይ ሳይሆን በሰዎች ልማድና በዚህ አለም መሠረታዊ ሕግጋት ላይ በተመሠረተ ፍልስፍና ከንቱ ማግባቢያ ማንም ማርኮ እንዳይወስዳችሁ ተጠንቀቁ” ቆላስይያስ 2÷8 አይገርምም ከንቱ ማግባቢያ ሰው ሠራሽ ዕውቀት አለማዊ ዕይታ ከንቱ ቢሆን እንኳ ሰውን የማማለል የመማረክ አቅም አለው አሁን ገባኝ የቆምኩበት አለም እና ቦታ ነበር ያጠመደኝ ቦታዬ ስለተቀየረ ቦታሽ አልገባኝም ሐሳቤ ስለተቀየረ ሐሳብሽ አንደቀድሞ አልገዛኝም በዚህ አለም ዕውቀት ሰው የሐሳቡ ውጤት ነው ይባል አይደል መፅሐፍ ቅዱስ ደግሞ “እንደ ስጋ ፈቃድ የሚኖሩ የስጋን ነገር ያስባሉና እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ” ሮሜ 8÷5
    ህናም ይህን ፅሁፍሽን ሳነበው አሁንም ለሐሳቤ ለክርስትናዬ የማይመጥን ከንቱ ሐሳብ ነው የቃላት ስብጥሮችሽ ሐሳብሸን ለማስዋብ የሞከርሽበት መንገድ ለማጓጓት ይሞክራሉ ግን ህይወት የላቸውም ክርስቶስን ወደ ማወቅ አይገፉም እንደውም ከህይወት ያጎድላሉ በተለመደው ድፍረትሽ ቤተክርስቲያንን ለመንቀፍ የሄድሽበት መንገድ ቤተክርስቲያንን ያቆዩልንን የዕምነት አባቶችን እንድንዳፈር ከመገፋፋት ያለፈ እውነት የለውም ቤተክርስቲያን የገሀነም ደጆች የማይቋቋማት የክርስቶስ ሙላት የሚገለጥባት እንጂ ተቋም አልያም ድርጅት አይደለችም ብትደክምም ብትበረታም ባለቤት አላት ከዚሁ ጋር አያይዤ አንቺ እንደደፈርሽው በድፍረት የምነግርሽ ቤተክርስቲያንን ለመዝለፍ ብቁ አለመሆንሽን ነው
    መፅሐፍ ቅዱስን ለመተርጎም የሄድሽበት መንገድ ግዜ ወስዶ ላላጠናው ሰው መሰናከያ ይሆናል ግዜ ለወሰደ ሰው ግን ሰህተቱ የተገለጠ ነው
    አንቺ በተለየ ትኩረት ከተመለከትሽው እና ተገለጠልኝ ብለሽ ካቶከርሽበት የገላትያው ክፍል በአንቺ የአተረጓገም ሂደት ተከትዬ እንዲህስ መተርጎም ይቻላል ወይ ብዬ ልጠይቅሽ እፈልጋለሁ
    ለብዙሃኑ ግብረሰዶማዊነት ርኩሰት አጢያት የሞራል ውድቀት ነው ለአድራጊዎቹ ግን በሁለት ወንዶች መሐከል ያለ የፍቅር ግንኙነት አልያም በሁሉት ሴቶች መሐከል ያለ የፍቅር ግንኙነት ነው አንደውም መፈክራቸው love is love የሚል ነው በውጪው አለም በክርስትና ዕምነት ውስጥ ተለጥፈው ፍቅር ብለው የሚጠሩትን ርኩሰት ዕውቅና ሊያሰጡት እንደሚጥሩ የታወቀ ነው እና በገላትያ ውስጥ ከተገለጡት የመንፈስ ፍሬዎች አንዱ ፍቅር ነው ስለዚህ በግብረሰዶም ውስጥ ያሉ ሰዎች የአንቺን የአተረጓገም ሂደት ተከትለው ፍቅር የመንፈስ ፍሬ ነው ከፍቅር ጋር የሚጣረስ ሕግ የለም ብለው ፍቅር ብለው ለሚሰይሙት ርኩሰት ዕውቅናን በቤተክርስቲያን ውስጥ ቢጠይቁ ልክ ነው ብለሽ ትቀበያቸዋለሽ ? ፍቅር ነው ብለሽ ትባርኪያቸዋለሽ ? ባትወልዱም በጉዲፈቻ ታሳድጋላችሁ ብለሽ ትመርቂያቸዋለሽ ? የእግዚአብሔርን እውነት በዓመፃ በማፈን በሰው ሰራሽ ሐሳብ ከወደቀ አለም በሚመነጭ ዕውቀት እንዲያምፁ ታበረታችያቸዋለሽ ?
    ብዙ ብዙ ልልሽ እችላለሁ ስሜታችን የሚነግረንን ሁሉ አናወራም የሚመስለንን አንፅፍም የምንመኘው ሁሉ ትክክል አይደለም ወጣ እና ለየት ያለ ሐሳብ ያለ ሲመስለን ልክ መሆናችንን አይመሰክርልንም አዋቂነታችንን አይገልጥም ከንግግራችን ይልቅ ዝምታችን ራስ መግዛታችንን ሊመሰክር ሰውን ሊያንፅ ይችላል ለዚህ ምሳሌ የምትሆነኝ ጓደኛሽ ቸሊና ናት ፀጥታዋ አለመጮዃ ትኩረት አለመፈለጓ እንዴት ለትምህርት እንደሆነኝ ዘመኑ ይህን ባያደንቅም ። ለብቻችን ስናስበው ያስመረቀነን ዕውቀት የተገለጠልን ሊመስሉ የሚችሉ ነገሮችን በሰው ፊት አናቀርበውም ምክንያቱም ስንፍናችንን ያጋልጥብናል አልያም መሬት ባረገጠ ቁንፅል ሐሳባችን ሰውን እናሰናክላለን ለምንፅፈው ለምናወራው አላፊነት መውሰድ የበሰለ ሰው ማሳያ ነው እንጂ በራስ መተማመን ማጣት አይደለም ዝምታ ወርቅ የሚሆንበት ግዜ ብዙ ነው በተለይ በዚህ ዘመን ።
    እኔ ግን ለትውልድ ግድ እንደሚለው ክርስቲያን ሰው ተፅህኖ ፈጣሪ ወንጌልን እንጅ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰውን እንደማይከተል ክርስቲያን ሐሳብሸን አጥብቄ እቃወማለሁ ዘፈን አጢያት ነው የእግዚአብሔር እውነት ! ይህን እውነት በሃመፃ ማፈንን አጥብቄ እቃወማለሁ እቃወምሻለሁ ክርስትና ይህን አያስተምርምና ።
    እውነትን በዓመፃ በሚከለክሉ ሰዎች በአጢያተኛነታቸውና በዓመፃቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ከሰማይ ይገለጣልና ሮሜ 1÷18

    • ***
      By Endashaw
      December 29, 2022 at 12:52 pm
      ስለ ዘፈን ለዘሪቱ ከበደ
      በዓለም እየተሳብኩ ስመጣ ዘፈን መውደድ ሲጀማምረኝ ለመጀመሪያ ግዜ ከቮይስ ሙዚቃ ቤት የገዛሁት የአንቺን ዘፈን ነበር ያኔ 17 አመቴ ነበረ ክርስቲያን እና የክርስቲያን ቤተሰብ ልጅ እንደመሆኔ ቤት ውስጥ በነበረው አንድ ቴፕ ተደብቄ እሰማሻለው ዕድሜዬ ሲጨምር የአለም ተፅህኖ በህኔ ላይ ሲበረታ አለማዊነቴ እና አለምን መውደዴ ገሀድ እየወጣ መጣ ያዳቆነ ሠይጣን እንደሚባለው አይነት ዘፈኖችሽን በመውደድ የተጀመረው አድማጭነቴ ወደ አክራሪ አድናቂነት የሐሳቦችሽ ተገዢ ጥግ የሌለው አድናቆት ተጠናወተኝ የዘፈንሽ ብቻ አይደለም የሐሳብሽ ታሳሪ አየሆንኩ መጣሁ በህኔ መጠን የሚያደንቅሽ ካለ እንጃ ዙሪያዬ ባሉ ሰዎች ቤተሰቦች ሁሉ በአንቺ ጉዳይ የታወቅሁ ነበርኩ ሽንጤን ይዤ ነበር ለዘፈንሽ እና ሐሳብሽ ምከራከር የነበረው እንዲህ እላለሁ ስገልፅሽ ዘሪቱ ሁሉ ነገር አላት ስታይሊሽ ናት ትደንሳለች ገጣሚ ናት ዜማ ታውቃለች ሐሳቧን መግለጥ አትፈራም ሙሉ ናት እላለሁ
      ያለፈው አልፎ አለምን ከመውደድ የተነሳ የህይወት ኪሳራ ውስጥ ገብቼ እያለሁ ኢየሱስ ከአለም ከጨለማ ከራሴ ዳግም በደሙ ዋጀኝ በምህረቱ ባለጠጋ ነውና በአዲሱ ሰውነት ውስጥ ለሁለት አመት ስኖር ጌታ በእግሮቼ ስር ካስረገጠኝ የአለም ከንቱ ነገሮች አንዱ ቀላል የሆነልኝ አጅግ የምወደው የገዛኝ የነበረውን ዘፈን ነው
      ጌታዬን ኢየሱስን በተቀበልኩ ብዙም ሳልጠነክር አስቀድሜ የምወደውን ዩትዩብ ላይ ከፋትሱ ጋር ያደረግሽውን ቃለመጠይቅ አየሁት ግን እንደበፊቱ አልወደድኩትም ትርጉምም አልሰጠኝም ራሴን እጠይቃለሁ ራሴን ለማፅደቅ እየሞከርኩ ነው ? ፅንፍ እየያዝኩ ነው ? ዘፋኝ የሆነችውን አስቀድሞ የምወዳትን ዘሪቱን ልጠላት እየሞከርኩ ነው ? እያልኩ ቃለመጠየቁን አየዋለሁ ፍፁም ትርጉም አልሠጠኝም እንደ ፍልስፍና የማየው አስቀድሞ የምመሰጥበት ከድፍረት ንግግሮችሽ አንዱ የሆነውን ኢየሱስ ሙዚቃ አይጠላም የሚለውን ወደ ልቤ ላቀርበው ብሞክርም አልሆነልኝም ቪዲዬውን እያየሁ ለምን አልተመሰጥኩበትም እንደቀድሞው ? እላለሁ ይህን እያሰብኩ በውስጤ ይህን ቃል ሰማሁት “በክርስቶስ ላይ ሳይሆን በሰዎች ልማድና በዚህ አለም መሠረታዊ ሕግጋት ላይ በተመሠረተ ፍልስፍና ከንቱ ማግባቢያ ማንም ማርኮ እንዳይወስዳችሁ ተጠንቀቁ” ቆላስይያስ 2÷8 አይገርምም ከንቱ ማግባቢያ ሰው ሠራሽ ዕውቀት አለማዊ ዕይታ ከንቱ ቢሆን እንኳ ሰውን የማማለል የመማረክ አቅም አለው አሁን ገባኝ የቆምኩበት አለም እና ቦታ ነበር ያጠመደኝ ቦታዬ ስለተቀየረ ቦታሽ አልገባኝም ሐሳቤ ስለተቀየረ ሐሳብሽ አንደቀድሞ አልገዛኝም በዚህ አለም ዕውቀት ሰው የሐሳቡ ውጤት ነው ይባል አይደል መፅሐፍ ቅዱስ ደግሞ “እንደ ስጋ ፈቃድ የሚኖሩ የስጋን ነገር ያስባሉና እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ” ሮሜ 8÷5
      ህናም ይህን ፅሁፍሽን ሳነበው አሁንም ለሐሳቤ ለክርስትናዬ የማይመጥን ከንቱ ሐሳብ ነው የቃላት ስብጥሮችሽ ሐሳብሸን ለማስዋብ የሞከርሽበት መንገድ ለማጓጓት ይሞክራሉ ግን ህይወት የላቸውም ክርስቶስን ወደ ማወቅ አይገፉም እንደውም ከህይወት ያጎድላሉ በተለመደው ድፍረትሽ ቤተክርስቲያንን ለመንቀፍ የሄድሽበት መንገድ ቤተክርስቲያንን ያቆዩልንን የዕምነት አባቶችን እንድንዳፈር ከመገፋፋት ያለፈ እውነት የለውም ቤተክርስቲያን የገሀነም ደጆች የማይቋቋማት የክርስቶስ ሙላት የሚገለጥባት እንጂ ተቋም አልያም ድርጅት አይደለችም ብትደክምም ብትበረታም ባለቤት አላት ከዚሁ ጋር አያይዤ አንቺ እንደደፈርሽው በድፍረት የምነግርሽ ቤተክርስቲያንን ለመዝለፍ ብቁ አለመሆንሽን ነው
      መፅሐፍ ቅዱስን ለመተርጎም የሄድሽበት መንገድ ግዜ ወስዶ ላላጠናው ሰው መሰናከያ ይሆናል ግዜ ለወሰደ ሰው ግን ሰህተቱ የተገለጠ ነው
      አንቺ በተለየ ትኩረት ከተመለከትሽው እና ተገለጠልኝ ብለሽ ካቶከርሽበት የገላትያው ክፍል በአንቺ የአተረጓገም ሂደት ተከትዬ እንዲህስ መተርጎም ይቻላል ወይ ብዬ ልጠይቅሽ እፈልጋለሁ
      ለብዙሃኑ ግብረሰዶማዊነት ርኩሰት አጢያት የሞራል ውድቀት ነው ለአድራጊዎቹ ግን በሁለት ወንዶች መሐከል ያለ የፍቅር ግንኙነት አልያም በሁሉት ሴቶች መሐከል ያለ የፍቅር ግንኙነት ነው አንደውም መፈክራቸው love is love የሚል ነው በውጪው አለም በክርስትና ዕምነት ውስጥ ተለጥፈው ፍቅር ብለው የሚጠሩትን ርኩሰት ዕውቅና ሊያሰጡት እንደሚጥሩ የታወቀ ነው እና በገላትያ ውስጥ ከተገለጡት የመንፈስ ፍሬዎች አንዱ ፍቅር ነው ስለዚህ በግብረሰዶም ውስጥ ያሉ ሰዎች የአንቺን የአተረጓገም ሂደት ተከትለው ፍቅር የመንፈስ ፍሬ ነው ከፍቅር ጋር የሚጣረስ ሕግ የለም ብለው ፍቅር ብለው ለሚሰይሙት ርኩሰት ዕውቅናን በቤተክርስቲያን ውስጥ ቢጠይቁ ልክ ነው ብለሽ ትቀበያቸዋለሽ ? ፍቅር ነው ብለሽ ትባርኪያቸዋለሽ ? ባትወልዱም በጉዲፈቻ ታሳድጋላችሁ ብለሽ ትመርቂያቸዋለሽ ? የእግዚአብሔርን እውነት በዓመፃ በማፈን በሰው ሰራሽ ሐሳብ ከወደቀ አለም በሚመነጭ ዕውቀት እንዲያምፁ ታበረታችያቸዋለሽ ?
      ብዙ ብዙ ልልሽ እችላለሁ ስሜታችን የሚነግረንን ሁሉ አናወራም የሚመስለንን አንፅፍም የምንመኘው ሁሉ ትክክል አይደለም ወጣ እና ለየት ያለ ሐሳብ ያለ ሲመስለን ልክ መሆናችንን አይመሰክርልንም አዋቂነታችንን አይገልጥም ከንግግራችን ይልቅ ዝምታችን ራስ መግዛታችንን ሊመሰክር ሰውን ሊያንፅ ይችላል ለዚህ ምሳሌ የምትሆነኝ ጓደኛሽ ቸሊና ናት ፀጥታዋ አለመጮዃ ትኩረት አለመፈለጓ እንዴት ለትምህርት እንደሆነኝ ዘመኑ ይህን ባያደንቅም ። ለብቻችን ስናስበው ያስመረቀነን ዕውቀት የተገለጠልን ሊመስሉ የሚችሉ ነገሮችን በሰው ፊት አናቀርበውም ምክንያቱም ስንፍናችንን ያጋልጥብናል አልያም መሬት ባረገጠ ቁንፅል ሐሳባችን ሰውን እናሰናክላለን ለምንፅፈው ለምናወራው አላፊነት መውሰድ የበሰለ ሰው ማሳያ ነው እንጂ በራስ መተማመን ማጣት አይደለም ዝምታ ወርቅ የሚሆንበት ግዜ ብዙ ነው በተለይ በዚህ ዘመን ።
      እኔ ግን ለትውልድ ግድ እንደሚለው ክርስቲያን ሰው ተፅህኖ ፈጣሪ ወንጌልን እንጅ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰውን እንደማይከተል ክርስቲያን ሐሳብሸን አጥብቄ እቃወማለሁ ዘፈን አጢያት ነው የእግዚአብሔር እውነት ! ይህን እውነት በሃመፃ ማፈንን አጥብቄ እቃወማለሁ እቃወምሻለሁ ክርስትና ይህን አያስተምርምና ።
      እውነትን በዓመፃ በሚከለክሉ ሰዎች በአጢያተኛነታቸውና በዓመፃቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ከሰማይ ይገለጣልና ሮሜ 1÷18

  • ***
    By Endashaw
    December 29, 2022 at 12:52 pm
    ስለ ዘፈን ለዘሪቱ ከበደ
    በዓለም እየተሳብኩ ስመጣ ዘፈን መውደድ ሲጀማምረኝ ለመጀመሪያ ግዜ ከቮይስ ሙዚቃ ቤት የገዛሁት የአንቺን ዘፈን ነበር ያኔ 17 አመቴ ነበረ ክርስቲያን እና የክርስቲያን ቤተሰብ ልጅ እንደመሆኔ ቤት ውስጥ በነበረው አንድ ቴፕ ተደብቄ እሰማሻለው ዕድሜዬ ሲጨምር የአለም ተፅህኖ በህኔ ላይ ሲበረታ አለማዊነቴ እና አለምን መውደዴ ገሀድ እየወጣ መጣ ያዳቆነ ሠይጣን እንደሚባለው አይነት ዘፈኖችሽን በመውደድ የተጀመረው አድማጭነቴ ወደ አክራሪ አድናቂነት የሐሳቦችሽ ተገዢ ጥግ የሌለው አድናቆት ተጠናወተኝ የዘፈንሽ ብቻ አይደለም የሐሳብሽ ታሳሪ አየሆንኩ መጣሁ በህኔ መጠን የሚያደንቅሽ ካለ እንጃ ዙሪያዬ ባሉ ሰዎች ቤተሰቦች ሁሉ በአንቺ ጉዳይ የታወቅሁ ነበርኩ ሽንጤን ይዤ ነበር ለዘፈንሽ እና ሐሳብሽ ምከራከር የነበረው እንዲህ እላለሁ ስገልፅሽ ዘሪቱ ሁሉ ነገር አላት ስታይሊሽ ናት ትደንሳለች ገጣሚ ናት ዜማ ታውቃለች ሐሳቧን መግለጥ አትፈራም ሙሉ ናት እላለሁ
    ያለፈው አልፎ አለምን ከመውደድ የተነሳ የህይወት ኪሳራ ውስጥ ገብቼ እያለሁ ኢየሱስ ከአለም ከጨለማ ከራሴ ዳግም በደሙ ዋጀኝ በምህረቱ ባለጠጋ ነውና በአዲሱ ሰውነት ውስጥ ለሁለት አመት ስኖር ጌታ በእግሮቼ ስር ካስረገጠኝ የአለም ከንቱ ነገሮች አንዱ ቀላል የሆነልኝ አጅግ የምወደው የገዛኝ የነበረውን ዘፈን ነው
    ጌታዬን ኢየሱስን በተቀበልኩ ብዙም ሳልጠነክር አስቀድሜ የምወደውን ዩትዩብ ላይ ከፋትሱ ጋር ያደረግሽውን ቃለመጠይቅ አየሁት ግን እንደበፊቱ አልወደድኩትም ትርጉምም አልሰጠኝም ራሴን እጠይቃለሁ ራሴን ለማፅደቅ እየሞከርኩ ነው ? ፅንፍ እየያዝኩ ነው ? ዘፋኝ የሆነችውን አስቀድሞ የምወዳትን ዘሪቱን ልጠላት እየሞከርኩ ነው ? እያልኩ ቃለመጠየቁን አየዋለሁ ፍፁም ትርጉም አልሠጠኝም እንደ ፍልስፍና የማየው አስቀድሞ የምመሰጥበት ከድፍረት ንግግሮችሽ አንዱ የሆነውን ኢየሱስ ሙዚቃ አይጠላም የሚለውን ወደ ልቤ ላቀርበው ብሞክርም አልሆነልኝም ቪዲዬውን እያየሁ ለምን አልተመሰጥኩበትም እንደቀድሞው ? እላለሁ ይህን እያሰብኩ በውስጤ ይህን ቃል ሰማሁት “በክርስቶስ ላይ ሳይሆን በሰዎች ልማድና በዚህ አለም መሠረታዊ ሕግጋት ላይ በተመሠረተ ፍልስፍና ከንቱ ማግባቢያ ማንም ማርኮ እንዳይወስዳችሁ ተጠንቀቁ” ቆላስይያስ 2÷8 አይገርምም ከንቱ ማግባቢያ ሰው ሠራሽ ዕውቀት አለማዊ ዕይታ ከንቱ ቢሆን እንኳ ሰውን የማማለል የመማረክ አቅም አለው አሁን ገባኝ የቆምኩበት አለም እና ቦታ ነበር ያጠመደኝ ቦታዬ ስለተቀየረ ቦታሽ አልገባኝም ሐሳቤ ስለተቀየረ ሐሳብሽ አንደቀድሞ አልገዛኝም በዚህ አለም ዕውቀት ሰው የሐሳቡ ውጤት ነው ይባል አይደል መፅሐፍ ቅዱስ ደግሞ “እንደ ስጋ ፈቃድ የሚኖሩ የስጋን ነገር ያስባሉና እንደ መንፈስ ፈቃድ የሚኖሩ ግን የመንፈስን ነገር ያስባሉ” ሮሜ 8÷5
    ህናም ይህን ፅሁፍሽን ሳነበው አሁንም ለሐሳቤ ለክርስትናዬ የማይመጥን ከንቱ ሐሳብ ነው የቃላት ስብጥሮችሽ ሐሳብሸን ለማስዋብ የሞከርሽበት መንገድ ለማጓጓት ይሞክራሉ ግን ህይወት የላቸውም ክርስቶስን ወደ ማወቅ አይገፉም እንደውም ከህይወት ያጎድላሉ በተለመደው ድፍረትሽ ቤተክርስቲያንን ለመንቀፍ የሄድሽበት መንገድ ቤተክርስቲያንን ያቆዩልንን የዕምነት አባቶችን እንድንዳፈር ከመገፋፋት ያለፈ እውነት የለውም ቤተክርስቲያን የገሀነም ደጆች የማይቋቋማት የክርስቶስ ሙላት የሚገለጥባት እንጂ ተቋም አልያም ድርጅት አይደለችም ብትደክምም ብትበረታም ባለቤት አላት ከዚሁ ጋር አያይዤ አንቺ እንደደፈርሽው በድፍረት የምነግርሽ ቤተክርስቲያንን ለመዝለፍ ብቁ አለመሆንሽን ነው
    መፅሐፍ ቅዱስን ለመተርጎም የሄድሽበት መንገድ ግዜ ወስዶ ላላጠናው ሰው መሰናከያ ይሆናል ግዜ ለወሰደ ሰው ግን ሰህተቱ የተገለጠ ነው
    አንቺ በተለየ ትኩረት ከተመለከትሽው እና ተገለጠልኝ ብለሽ ካቶከርሽበት የገላትያው ክፍል በአንቺ የአተረጓገም ሂደት ተከትዬ እንዲህስ መተርጎም ይቻላል ወይ ብዬ ልጠይቅሽ እፈልጋለሁ
    ለብዙሃኑ ግብረሰዶማዊነት ርኩሰት አጢያት የሞራል ውድቀት ነው ለአድራጊዎቹ ግን በሁለት ወንዶች መሐከል ያለ የፍቅር ግንኙነት አልያም በሁሉት ሴቶች መሐከል ያለ የፍቅር ግንኙነት ነው አንደውም መፈክራቸው love is love የሚል ነው በውጪው አለም በክርስትና ዕምነት ውስጥ ተለጥፈው ፍቅር ብለው የሚጠሩትን ርኩሰት ዕውቅና ሊያሰጡት እንደሚጥሩ የታወቀ ነው እና በገላትያ ውስጥ ከተገለጡት የመንፈስ ፍሬዎች አንዱ ፍቅር ነው ስለዚህ በግብረሰዶም ውስጥ ያሉ ሰዎች የአንቺን የአተረጓገም ሂደት ተከትለው ፍቅር የመንፈስ ፍሬ ነው ከፍቅር ጋር የሚጣረስ ሕግ የለም ብለው ፍቅር ብለው ለሚሰይሙት ርኩሰት ዕውቅናን በቤተክርስቲያን ውስጥ ቢጠይቁ ልክ ነው ብለሽ ትቀበያቸዋለሽ ? ፍቅር ነው ብለሽ ትባርኪያቸዋለሽ ? ባትወልዱም በጉዲፈቻ ታሳድጋላችሁ ብለሽ ትመርቂያቸዋለሽ ? የእግዚአብሔርን እውነት በዓመፃ በማፈን በሰው ሰራሽ ሐሳብ ከወደቀ አለም በሚመነጭ ዕውቀት እንዲያምፁ ታበረታችያቸዋለሽ ?
    ብዙ ብዙ ልልሽ እችላለሁ ስሜታችን የሚነግረንን ሁሉ አናወራም የሚመስለንን አንፅፍም የምንመኘው ሁሉ ትክክል አይደለም ወጣ እና ለየት ያለ ሐሳብ ያለ ሲመስለን ልክ መሆናችንን አይመሰክርልንም አዋቂነታችንን አይገልጥም ከንግግራችን ይልቅ ዝምታችን ራስ መግዛታችንን ሊመሰክር ሰውን ሊያንፅ ይችላል ለዚህ ምሳሌ የምትሆነኝ ጓደኛሽ ቸሊና ናት ፀጥታዋ አለመጮዃ ትኩረት አለመፈለጓ እንዴት ለትምህርት እንደሆነኝ ዘመኑ ይህን ባያደንቅም ። ለብቻችን ስናስበው ያስመረቀነን ዕውቀት የተገለጠልን ሊመስሉ የሚችሉ ነገሮችን በሰው ፊት አናቀርበውም ምክንያቱም ስንፍናችንን ያጋልጥብናል አልያም መሬት ባረገጠ ቁንፅል ሐሳባችን ሰውን እናሰናክላለን ለምንፅፈው ለምናወራው አላፊነት መውሰድ የበሰለ ሰው ማሳያ ነው እንጂ በራስ መተማመን ማጣት አይደለም ዝምታ ወርቅ የሚሆንበት ግዜ ብዙ ነው በተለይ በዚህ ዘመን ።
    እኔ ግን ለትውልድ ግድ እንደሚለው ክርስቲያን ሰው ተፅህኖ ፈጣሪ ወንጌልን እንጅ ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰውን እንደማይከተል ክርስቲያን ሐሳብሸን አጥብቄ እቃወማለሁ ዘፈን አጢያት ነው የእግዚአብሔር እውነት ! ይህን እውነት በሃመፃ ማፈንን አጥብቄ እቃወማለሁ እቃወምሻለሁ ክርስትና ይህን አያስተምርምና ።
    እውነትን በዓመፃ በሚከለክሉ ሰዎች በአጢያተኛነታቸውና በዓመፃቸው ሁሉ ላይ የእግዚአብሔር ቁጣ ከሰማይ ይገለጣልና ሮሜ 1÷18

  • “ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታል፤ ስለ እኔ ግን ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ያገኛታል።”
    ማቴዎስ 16፥25
    ተሰጥሆዋቸውን መተው የማይችሉ ነብሳቸውን እንዴት ሊያጠፋ ይችላሉ ?

SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.