
በዓለ ጰራቅሊጦስ
በኢትዮጵያ ከ1555-1585 ዓ.ም. የነገሠው የዐፄ ሠርጸ ድንግል ዜና መዋዕል ጸሐፍት ዜና መዋዕሉን መጻፍ የጀመሩት የሚከተለውን ጸሎት በማቅረብ ነበር። “ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ አስተብቍዖ ወሰአሎ ለእግዚአብሔር አቡከ ከመ ይፈኑ ላዕሌነ ጰራቅሊጦስሃ መንፈሰ ጽድቅ ዘኢይክል ዓለም ነሢኦቶ። ወመጺኦ ውእቱ ይመርሐነ ኀበ ኵሉ ጽድቀ ነገር። እስመ አይነግር እም ኀቤሁ ፈጠራ ወሐሰት አምሳለ ካልኣን መናፍስት እለ አልቦ ጽድቀ[ቅ] ውስተ አፉሆሙ። – ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ዓለም ሊቀበለው የማይችለውን የእውነት መንፈስ የኾነውን ጰራቅሊጦስን ይልክን ዘንድ የባሕርይ አባትኽን እግዚአብሔርን ማልደው፤ ለምነውም። መጥቶም ወደ እውነት ነገር ኹሉ ይመራናልና፤ በአፋቸው ውስጥ እውነት እንደሌላቸው እንደ ሌሎች መናፍስት የሐሰትን ነገር ከራሱ አንቅቶ አይናገርምና” (የዐፄ ሠርጸ ድንግል ዜና መዋዕል 1999፣ 3)።
4 comments
በጎ ምክር ይመስላል። ከእውነታው ጋር ግን አልተገናዘበም። ሕዝቡ መልካም፣ መሪና ሊኂቃኑ ነው ችግሩ ማለት ጨርሶ ስህተት ነው። የሚሰማ ጆሮ ሲኖረን ሁሉ ይቃለላል ማለት ውስብስቡን ማቅለል ነው።
ጸሐፊው ያለውን ሰጠን። ታዲያ እንደርስዎ ምን ይሻለናል?
– ችግሩ ሕዝብ ነው ባይ ነዎት?
– ውስብስቡ ተቃለለ ያሉት ችግርና መፍትሔው ምንድነው? … ይሉናል? (መልስዎን በአክብሮት እጠብቃለሁ)
እውነት ጥሩ ጥያቄዎች ናቸው!
አሜን ጆሮ ያለው ይስማ። ጸጋውን ያብዛልህ ውድ ወንድሜ።
_________ እኔም ከአንተ ጋር
“ሲጀመር የሚሰማ ጆሮ ይኑረን። መሰማት ያለበትን አስቀድመን እንስማ። የሕዝብ ጆሮ ሰሚ ያጣውን ፈጣሪ ለመስማት ይከፈት። የልኂቃን ጆሮ ሰሚ ያጣውን ሕዝብ ለመስማት ይከፈት። ያንን ከሰማን ወደ እርስ በርስ መደማመጥ እንመጣለን። ስንደማመጥ ደግሞ ወደ መግባባት እንደርሳለን። ስንግባባ ዐብረን እንደ አንድ ሆነን እንቆማለን። አንድ ላይ አንድ ሆነን ስንቆም፣ ያኔ ከመድኃኒታችን ጋር እንገናኛለን። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።”
እላለሁ።