
ነውር የሌለው አምልኮ
በኢንተርናሽናል ኢቫንጀሊካል ቤተ ክርስቲያን ከሚያዚያ 2–3፣2006 ዓ.ም.“ጉባኤ ስለ ወላጅ አጥ ልጆች በኢትዮጵያ፡- ሀገራዊ ጥሪ ለሀገራዊ መፍትሔ” በሚል መሪ ቃል ጉባኤ ተካሄዶ ነበር። ጉባኤውን ያዘጋጁት “ቤታኒ ክርስቲያን ሰርቪስስ”፣ “ሜክ ዩር ማርክ”፣ “ቅድሚያ ፋውንዴሽን”፣ “የልጆች ዕድገት ሥልጠናና ምርምር ማዕከል” እንዲሁም “አባት ለሌላቸው ብሩኅ ተስፋ” ሲሆኑ፣ ድርጅቶቹም በልጆች አገልግሎት ዙሪያ የተለያየ እንቅስቃሴ የሚያደርጉ ሀገር በቀልና ዓለም አቀፍ ተቋማት ናቸው። በዝግጅቱ ላይ 470 የሚደርሱ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን፣ የተለያዩ ቤተ ሰቦች እና ለልጆች ልዩ ሸክም ያላቸው ወገኖች እንደታደሙ ከአዘጋጆቹ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
Add comment