[the_ad_group id=”107″]

ሚዲያውን ቸል አንበለው!

ለወንጌል ሥራ ስላለው ጠቃሜታ ብዙ የተባለለት የብዙኀን መገናኛ በእኛ አገር የአቅሙን ያህል እንዳልተጠቀምንበት ለብዙዎች የተሰወረ አይደለም፡፡ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች አንድም ከግንዛቤ ጉድለት፣ አንድም ደግሞ ከፍላጎት ማጣት የተነሣ ቸል ያሉት ይህ የአገልግሎት ዘርፍ አሁን ከመቼውም ጊዜ በላይ አስፈላጊነቱ ጎልቶ እየታየ መጥቷል፡፡

ይህንን የተረዱ ጥቂት ግለ ሰቦችና ቤተ ክርስቲያናት የአገልግሎት ዘርፉን ተቀላቅለው ደፋ ቀና እያሉ ይገኛሉ፡፡ “ጥቂት” የምንለው አማኝ ማኅበረ ሰቡ ካለው ቁጥር አንጻር ሲታይ አሁን ያሉት (የነበሩትን ጨምሮ) የክርስቲያን ሚዲያ አባላት እጅግ አነስተኛ ከመሆናቸው የተነሣ ነው፡፡ እነዚሁ ግለ ሰቦችና ተቋማት የበኩላቸውን ጥረት ቢያደርጉም እንኳ ሊደርሱት ከሚፈልጉት ሕዝብ አነጻር ውጤታማነታቸው ያን ያህል አመረቂ ስለመሆኑ በርግጠኝነት መናገር አይቻልም፡፡ ከዚያም ባለፈ የሠሯቸውና እየሠሯቸው ያሉ ስሐተቶች ብዙዎች የአገልግሎት ዘርፉን እንዲፈሩት፣ እንዲሸሹት ብሎም እንዲጠሉት ሳያደርገው አልቀረም፡፡

ሕንጸት መጽሔት የአገልግሎት ዘርፉን፣ በተለይም ደግሞ የቴሌቪዥን አገልግሎቱን ርእሰ ጉዳይ አድርጎ ያነሣበት ዋናው ምክንያት ዘርፉ ያለበትን ድክመት በመጠቆም የተሻለ ደረጃ የሚያደርሰውን መንገድ ለመፈለግ ነው፡፡ ባሉብን ችግሮች ላይ በግልጽ መወያየት ካልቻልን፣ ችግሮቻችንን መቅረፍም ሆነ የተሻለ አገልግሎት መስጠት አንችልም ብለን በጽኑ እናምናለን፡፡ ስለሆነም፣ ርእሰ ጉዳዩ ይመለከተናል የሚሉ ማናቸውም አካላት፣ የኢትዮጵያ የክርስቲያን ብዙኀን መገናኛ አገልግሎትን ለማሳደግና የተሻለ ለማድረግ ኀላፊነት በተሞላው መልኩ እገዛ ሊያደርጉለት ይገባል፡፡ በአገልግሎት ዘርፉ የተሰማራን  ወገኖችም ያሉብንን ክፍተቶች ለመሙላት እስከዛሬ የመጣንበትን መንገድ መመርመር፣ ብሎም ከስሕተቶቻችን ለመማር ራሳችንን ትኁታን የማድረጊያው ጊዜ አሁን እንደ ሆነ በማመን ልንተጋ ያስፈልገናል፡፡

አለንጋ እና ልጓም

“በአግባቡ የተገራ ፈረስ ለባለቤቱ ክብር ያመጣል። ወደ ጦር ሜዳ ቢያደርስም፣ ዋንጫ ቢያሸንፍም፣ ታርሶበት ቢያመርትም፣ ግልቢያ ቢያሳምርም ትርፉና ክብሩ ለባለቤቱ ነው! . . . ሰው እንደ ፈረስ ነው። ያለ አለንጋና ያለ ልጓም አይኖርም። ልከኛው ባለአለንጋ ግን እግዚአብሔር ነው። ሲሻውም ልጓም ይሆናል።” ጳውሎስ ፈቃዱ።

ተጨማሪ ያንብቡ

One Nation of Sisters and Brothers

In this article, Dr Desta Heliso discusses shared national identity – an identity that formed the current Ethiopia. He argues that Ethiopianness is a unifying state of mind developed by people of different ethnic groups, cultural backgrounds and religious persuasions.

ተጨማሪ ያንብቡ

የወንጌላውያኑ መንታ መንገድ

የኢትዮጵያ ወንጌላዊው ክርስትና በአገሪቱ ከመቶ ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡ በተለያዩ ውጣ ውረዶች ውስጥ ያለፈው ይህ ሃይማኖታዊ ማኅበረ ሰብ በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ብሎም ፖለቲካዊ መስተጋብር ውስጥ የራሱን አሻራ እየተወ የመጣ መሆኑን መካድ አይቻልም፡፡ ይልቁኑም ደግሞ በአሁኑ ጊዜ እንደ ከዚህ ቀደሙ የተናቀ ማኅበረ ሰብ ሆኖ ላለመቀጠል በሚያደርገው ትግል እየተፈጠረ ያለው ለውጥ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ነው፡፡ ባለፉት ዐሥርት ዓመታት የተከሰተው ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያ ለውጥ በአገሪቱ ሃይማኖታዊ መስጋብር ላይ የራሱ የሆነ ተጽእኖ አሳድሯል፡፡ በዚህ ለውጥ ውስጥ ተጠቃሚም ተጎጂም መኖሩ አይቀርም፡፡ በአንዳንዶች ዘንድ ይህ ለውጥ ለወንጌላውያኑ ማኅበረ ሰብ የድል ብሥራት ይዞ እንደመጣ ሊታሰብ ይችላል፡፡ በርግጥ ይህ አስተሳሰብ እውነት የሚሆንባቸው ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላል፤ በአንጻሩም ያልተጠበቀ ውጤት አስከትሎ እንደ ሆነ ማሰቡ ተገቢ ነው፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ

Add comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.