
ኢየሱስ ክርስቶስን ማየትና መጠማት
አማረ ታቦር Seeing and Savoring Jesus Christ ከተሰኘው የጆን ፓይፐር መጽሐፍ መግቢያ የተወሰኑ አንቀጾችን ተርጉሞ እንደሚከተለው አቅርቧቸዋል።
[the_ad_group id=”107″]
የንጹሐን ደም በግፍና በጭከና እየፈሰሰ፣ የፍርሀትና የስጋት ጽልመት አገራችንን በሸፈነበት በዚህ ወቅት፣ ለፍትሕ የምናሰማው ጩኸት እንዳለ ሆኖ፣ እግዚአብሔር ዓለማትን በፈጠረበትና ደግፎ በያዘበት በዚያው የሥልጣኑ ቃል፣ አገራችንን በፍጹም ሉዓላዊነት ደግፎ እንደያዘ ልብ ልንል ይገባል። እርሱ ትላንትናን፣ ዛሬና ነገን በአንድ ጊዜ በእጁ የያዘ አምላክ ነው። ነገሥታት ነገን አያውቁም፤ ከሊቆችም የተሰወረ ነው። በርግጠኝነት የምናውቀው ግን፣ የእግዚአብሔርን ሁሉን ዐዋቂነት፣ ሁሉን ገዢነት፣ ቻይነትና ታማኝነት ነው። ፍርሀታችን፣ ጥያቄያችን፣ ስጋታችንና ተጋዳሮቶቻችን በሙሉ በእርሱ ዘንድ የታወቁ ናቸው። የአንዲቷም ሰኮንድ ኹነት (event) ከእርሱ ልትሰወር አትችልም።
የሰላም መረበሽና የፍትሕ ቀውስ እየከረረ በመጣበት በዚህ ዘመን፣ እንደ ክርስቲያን ተስፋ የምናደርገው የታሪክን አቅጣጫ በልጓም የያዘውን ልዑል እግዚአብሔርን ነው። ከእርሱ የፍትሕ ዐይኖች የሚሰወር ምንም ነገር የለም። እግዚአብሔር ከአቤል ዘመን ጀምሮ የንጹሐንን ደም ሲያፈስሱ ከነበሩት ግፈኞች ይልቅ እጅግ ብርቱ አምላክ ነው፤ ከዙፋኑ ፍርድ ይሰጣል። በገዛ ወንድሙ ከተገደለው ከአቤል ጀምሮ፣ በቅርቡ ዲያቢሎሳዊ በሆነ ጭከና እስከ ተገደሉት ወገኖቻች ድረስ የፈሰሰው የንጹሐን ደም በከንቱ አይቀርም። የቱንም ያህል ቢጨልም፣ አገራችን በልዑል እግዚአብሔር እጅ እንጂ፣ በግፈኞች እጅ አይደለችም።
ኢዮሣፍጥ በሁሉ አቅጣጫ ጦርነት በታወጀበትና ግራ በተጋባበት ጊዜ፦ “የአባቶቻችን አምላክ እግዚአብሔር ሆይ፤ አንተ በሰማይ የምትኖር አምላክ አይደለህምን? የምድር ሕዝቦችን መንግሥታት ሁሉ የምትገዛ አንተ ነህ፤ ኀይልና ሥልጣን በእጅህ ነው፤ ሊቋቋምህም የሚችል ማንም የለም።” በማለት ጸለየ (2 ዜና 20፥6)።
ወገኖቼ – እግዚአብሔር – አለ! አዎን አለ! ምንም እንኳን ከተከበበት የስጋት ጽልመት መውጫውን ባያውቅም፣ በእግዚአብሔር ሉዓላዊነትም በመደገፍ፣ ኢዮሣፍጥ እንዲህ አለ፦ “የመጣብንን ይህን ታላቅ ሰራዊት እንቋቋም ዘንድ አቅም የለንምና የምናደርገውን አናውቅም፤ ነገር ግን ዓይኖቻችን ወዳንተ ናቸው . . .” (2 ዜና 20፥12)።
እግዚአብሔርን ፈለገ፤ ተገኘለትም። “ሰልፉ የእኔ ነው፣ የማደርገውን ማዳን ተመልከት አለው።” ሁሉን ቻዩ ልዑል እንደተናገረው፣ ድብቅ ጦርን አስነሣ፤ ምድሪቱም አረፈች፤ በዙሪያው ካለው ስጋት ሁሉ አሳረፈው!
ለአገራችንም እንዲሁ ይሁንልን። አሜን!
Share this article:
አማረ ታቦር Seeing and Savoring Jesus Christ ከተሰኘው የጆን ፓይፐር መጽሐፍ መግቢያ የተወሰኑ አንቀጾችን ተርጉሞ እንደሚከተለው አቅርቧቸዋል።
ጸሐፊ፣ ተመራማሪ እና አስተማሪ የሆነው ምኒልክ አስፋው ከሚኖርበት አሜሪካ ሆኖ ስለ ፍትሕ እና ምሕርት/ይቅርታ ባዘጋጀው ጽሑፉ የዚህ ዕትም ዋና ርእሰ ጉዳይ ጸሐፊ ሆኖ ቀርቧል። ጽሑፉ በዋናነት ከፍትሕ እና ከምሕረት የትኛው የበለጠ ፋይዳ ያለው መሆኑን በመጠቆም የተሰናዳ ነው። ምኒልክ ለዚህ መነሻ የሚያደርገውም እውቁን የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት የነበሩትን ሟቹ ኔልሰን ማንዴላን ነው። እንደ እርሱ እምነት ከሆነ የማንዴላ የዕርቅ መንገድ በቅራኔ ለተሞላ ኅብረተ ሰብ ዐይነተኛ ምሳሌ ነው። ትልቅነት የሚለካውም ይቅር በሚሉና ምሕረት በሚያደርጉ ሰዎች የሕይወት ፈለግ መሆኑንም ይሞግታል።
In this article, Andrew DeCort (Dr.) argues that pluralism is vital if democracy should take the floor, in societies such as ours. He even says: “Advocating democracy without pluralism is like advocating fish without water. The one cannot live without the other.”
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment