[the_ad_group id=”107″]

የማንነት ስምምነት ካልቀደመ እየሠሩ ማፍረስ ይቀጥላል

በአጭሩ ግጭት ማለት “ቡድኖች የግብ ልዩነት ሲኖራቸው” ማለት ነው። ከዚህ አንጻር ከጥቂት ወራት በፊት የኢህአዴግ “ውስጥ ወለድ” ለውጥ፣ “ከውስጥ ወለድ ግጭት” በቀር በሁሉም ዘንድ ተቀባይ በማግኘቱ፣ ጎልቶ የወጣ የግብ ልዩነት ስላልነበረ የ“መደመር” ሂደቱን በአንጻራዊ ቀላል አድርጎት ነበር። ስለዚህ ኢህአዴግ ሲለወጥ (ቢያንስ ዋና ዋና ለውጦች አድርጓልና) ለውጡን የሚፈልጉ ሁሉ ‘ዐላማችን ግቡን መትቷል’ ማለት መቻል ይኖርባቸዋል።

አሁን የማንነት ጥያቄ የሚመለስበት፣ ተከድነው ይበስሉ የነበሩ ድስቶች እፊያቸው የሚነሣበት ወቅት በመሆኑ፣ ሁሉም የወጠወጠውን ገርበብ አርጎ ሲከፍት ጠረኑ እያወደ ነው። ማላከኮችና ማሳበቦች የሚነጻጸሩት “የማምለጫውን ፍየል” (scapegoating) በመፈለግ ሳይሆን፣ አሁን የታዩና እየታዩ ያሉ ክስተቶችን እንዲሁም ክስተቶቹን የወለዷቸውን ቀዳሚ ትርክቶች ተመሳሳይነት ከቡድኖች የቀድሞ ባሕርያት ጋር በማነጻጸር እና በማገናዘብ ነው። አንዳንዶች ያው ናቸው፤ ለአዲስ ተግባር የሚያስፈልግ አዲስ ባሕርይ እያሳዩ አይደለም። የባሕርይ ለውጦች በሌሉባቸው፣ የተግባር ለውጦች አይኖሩም! ባሕርያቸው ያልተለወጠ ቡድኖች፣ በሰላም የሚጎለብተውን አዲሱን ለውጥ “ያገሙታል”።

እንግዲህ አሁን የምናያቸው “ግጭቶች” መሠረታዊ የሆኑና በግልጽ ቋንቋ ወደ አደባባይ መምጣት ያለባቸው “የማንነት ትርጓሜ” ላይ ያሉ ልዩነቶች ናቸው። አልቸኮልኩም፤ አልፈረድኩም፤ ያስተዋልኩትን ነው የምናገረው።

ከኢትዮጵያዊ ማንነት አንጻር ቢያንስ ሦስት ቡድኖች አለ፦

  1. ኢትዮጵያዊነትን እንደ ማንነት ርእዮተ ዓለምም ሆነ፣ እንደ መፈክርም የሚቀበል። ይህ ቡድን ኢትዮጵያዊነትን በዐደራ እንደተቀበለው፣ መጠበቅ እንዳለበትና ለመጪውም ትውልድ ይህንኑ ማስተላለፍ እንዳለበት አምኖ ለዚህ ማንነት ይኖራል፤ ይሞታል።
  2. ኢትዮጵያዊነትን እንደ መፈክር የሚቀበል፣ እንደ ማንነት የሚያንገራግር፣ ግዴለሽ፣ “እናቴን ያገባ ሁሉ አባቴ ነው” ባይ አለ።
  3. ኢትዮጵያዊነትን እንደ ማንነት ርእዮተ ዓለምም ሆነ፣ እንደ መፈክር የማይቀበል ቡድን ደግሞ አለ። ይህ ቡድን ኢትዮጵያዊነትን የተጫነበት እንደ ሆነ የሚያስብ፣ እንደ ታሪካዊ ጠላት የሚያየው ስም፣ ከዚህ ጋር ንክኪ ያለውን ነገር ሁሉ ለማጥፋት የሚኖርና የሚሞት ነው። ለምን ኖረ አልልም፤ የታሪክ ሒደት ፈጥሮታልና። ይሁን እንጂ ተጨባጭ ሁኔታ ላይ የተመሠረት ይሁን አይሁን፣ በሚገባ መጣራት እንዲሁም ሰይፍ የሌለበት መፍትሔ ማግኘት ይኖርበታል።

እንደ አገር ግን እነዚህ ልዩነቶች ካልታረቁ መቀራቅሩ መልኩን ይቀይራል እንጂ የግጭቱ ዑደት ይቀጥላል (ይህ አይቀሬና አሳዛኝ እውነት ነው)። በማንነታችን ላይ እስካልተስማማን ድረስ እንደ ጅል እየሠራን ማፍረስ እና እየሞትን መኖር ይቀጥላል። እኛ ማነን? በዓለም አቀፉ ማኅበረ ሰብ፣ በአንድ ባንዲራ እየታወቅን በምድራችን በባንዲራ ብዛት ከተላለቅን የማንነት ቀውስ ይሏችኋል ይህ ነው። እኛ ማን ነን?

ኢየሱስ? ወይስ ሞት?

“በኢየሱስ የሆንን እኛ በሕይወት ነን፤ ማንም እርሱን በሕይወትነቱ ቢያውቀው በሕይወት ይኖራል። ሊያውቀው ባይወድድ ግን በሞት ይቀራል፤ መጨረሻውም ለዘላለም ከእግዚአብሔር የመለየት ቅጣት ይሆናል።” ዘሪቱ ከበደ

ተጨማሪ ያንብቡ

ፖሊካርፕ ያኔ፣ ፖሊካርፕ ዛሬ

የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን፣ የምሥራቅም የኦሪየንታል ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት፣ እንዲሁም የአንግሊካን እና የሉተራን አብያተ ክርስቲያናት በአንድ ድምጽ ”ቅዱስ” ሲሉ የሰየሙት ሰው ነው− ቅዱስ ፖሊካርፕ።

ተጨማሪ ያንብቡ

ዘመነ አስተርእዮ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዓመቱን በወቅቶች ከፋፍላ፥ በዚያ ላይ የተመሠረቱ መዝሙሮችን በግእዝ ለእግዚአብሔር በማቅረብና ድንቅ ሥራውን በመዘከር ትታወቃለች። ለዚህም በስድስተኛው ምእት ዓመት የተነሣው የዜማ ደራሲ ቅዱስ ያሬድ ከብሉያትና ከሐዲሳት (ከመጽሐፍ ቅዱስ)፣ ከሊቃውንትና ከመሳሰሉት መጻሕፍት ለምስጋናና ለጸሎት የሚስማሙ ንባባትን በመውሰድና ለዜማ ተስማሚ በማድረግ፥ በአራቱ ክፍላተ ዘመን እንዲነገሩ ማዘጋጀቱን የዜማ ሊቃውንት ያስረዳሉ (ጥዑመ ልሳን /ሊቀ ካህናት/ 1981፣ 28)። አራቱ ክፍላተ ዘመን የተባሉትም በዓመት ውስጥ የሚገኙት አራቱ ወቅቶች ናቸው፤ እነርሱም መፀው (ወርኀ ጽጌ ዘመነ ጽጌ/አበባ)፣ ሐጋይ (በጋ)፣ ጸደይ (በልግ) እና ክረምት ሲኾኑ፣ አኹን የምንገኘው ከአራቱ ክፍላተ ዘመን ኹለተኛው ክፍል በኾነው በበጋ (ሐጋይ) ላይ ነው።

ተጨማሪ ያንብቡ

Add comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.