
Christian Persecution And Genocide Is Worse Now Than “Any Time In History,” Report Says
A new report from a Catholic organization found that the persecution of Christians is worse “than at any time in history.
[the_ad_group id=”107″]
ሰሞኑን በተለይ በተኣምረ ማርያምና በገድለ ተክለ ሃይማኖት ውስጥ የተጻፉና መጽሐፍ ቅዱስን የሚቃረኑ ትምህርቶች ያስነሡት አቧራ ቀላል አይደለም። አቧራውን ያጫጨሰው ደግሞ በመጻሕፍቱ ላይ ለቀረበው ትችት ከዚህም ከዚያም ወገን እየተሰነዘሩ ያሉ ተገቢነት ያላቸውም የሌላቸውም አስተያየቶች ናቸው። አንዳንድ ጳጳሳትና የቤተ ክርስቲያኒቱ መምህራን የሚሰጧቸው እጅግ የወረዱና ከአባቶች የማይጠበቁ ተራና ቃላተ ጽርፈትን የተሞሉ አስተያየቶች ስሜት የወለዳቸውና አስገራሚም ናቸው፤ ምክንያቱም አንዳንዶቹ ተናጋሪዎች በገድላትና ድርሳናት ላይ ያላቸው አመለካከትና አቋም ይታወቃልና። ኾኖም ስንናገር በዚህ መንገድ መኾን የለበትም ሲሉ የተደመጡ አባቶችም አሉ። በዋናነትም ፓትርያርኩ ይጠቀሳሉ።
ከተነሣው ከዚህ ጕዳይ የተወለዱ ጠቃሚ ሐሳቦችም ያሉ ይመስላል። አንዱና ዋናው ቤተ ክርቲያኒቱ በስሟ በየመንደሩ በተከፈቱ ማተሚያ ቤቶች እየታተሙ የሚወጡትንና ቤተ ክርስቲያኒቱን የማይወክሉ ባለቻቸው መጻሕፍት ላይ፥ በሊቃውንት ጉባኤ በኩል የማጣራትና ገድላትና ድርሳናትን የማረምና የማስተካከል ሥራ እንደሚሠራ መነገሩ ነው። ነገር ግን ዮናታን ያነበባቸው መጻሕፍት በተለይ ተኣምረ ማርያምና ገድለ ተክለ ሃይማኖት በየመንደሩ የታተሙ ሳይኾኑ፥ በቤተ ክርስቲያኒቱ ዕውቅና የተሰጣቸውና በትንሣኤ ዘጉባኤ ማተሚያ ቤት የታተሙ ናቸውና፥ ስሕተቱን ሌሎች እንደ ፈጸሟቸው አስመስሎ ማቅረብ የራስን ስሕተት ለመሸፈን ካልኾነ በቀር እውነትነት የለውም።
አንዳንድ አባቶች ደግሞ ርእሰ ጕዳዩ በቤተ ክርስቲያኒቱ ዘንድ ከቀሰቀሰው ቍጣ ባሻገር፥ ጕዳዩ መነሣቱ እንድንነቃና ራሳችንን እንድንመለከት አድርጎናል የሚል መልክ ያለው አስተያየት ሲሰጡ ተደምጠዋል። ሌሎች ደግሞ ከዚህ በተቃራኒ ቆመው ገድላትና ድርሳናት ምንም ስሕተት እንደሌለባቸውና ስም አጥፊዎች አለአግባብ እንደ ተሣለቁባቸው፥ ስለዚህ መሻሻል እና/ወይም መታረም ሳያስፈልጋቸው መቀጠል እንደሚችሉ የሚያሳይ አቋም ያዘለ ማብራሪያ በቤተ ክርስቲያኒቱ ቴሌቪዥን ጭምር ቀርበው እየተናገሩ ነው። እንዲህ ሲያደርጉም መጽሐፍ ቅዱስን ባልተነገረበትና ባልተጻፈበት ዐውድ ጭምር እንዳሻቸው እየጠቀሱ ገድልን ከሐዋርያት ሥራ ጋር እስከ ማነጻጸር ደርሰው፥ ጥቅሶችን ባልተነገሩበት ዐውድም በመተርጐም ሲያደናግሩና ሲያምታቱ አስተውለናል።
አንድ ሐቅ አለ። መጽሐፍ ቅዱስ ታትሞ በብዙዎች እጅ ከመግባቱና ብዙዎች አንብበው ሕይወታቸው መለወጥ ከመጀመሩ በፊት፥ በየሰዉ እጅ ይገኙ የነበሩት፣ ሰዉም የተማረውና የተሰበከው ከገድላትና ከድርሳናት ነው። በአብዛኛው ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት ውስጥ የተሰበኩና ከአብዛኛው ሕዝብ ሕይወት ጋር የተዋሐዱትም እነርሱው ናቸው። በተለይም ፊደል ያልቈጠረውና የቈጠረውም ጭምር፥ በገጠርም በከተማም የሚኖረው ሕዝብ ለመጽሐፍ ቅዱስ እንግዳ ለገድላትና ለድርሳናት ወይም ለትምህርቶቻቸው ደግሞ ቅርብ ነው። የሚኖረውም ከእነርሱ እንደ ተሰበከውና እንደ ተማረው፥ በዋናነትም በቅዱሳን ስም ልዩ ልዩ ተግባራትን በመፈጸምና በቅዱሳኑ ስም በመማጸን መዳን አገኛለኹ ብሎ ነው። ከኹሉም በላይ ደግሞ እነዚህ መጻሕፍት በየቀኑ በቤተ ክርስቲያንና በግለ ሰቦችም ሥርዐተ አምልኮ የሚፈጸምባቸው የሥርዐተ አምልኮ ክፍል ናቸውና ከዚህ አንጻር ገድላትንና ድርሳናትን ማረም ቀላል ሥራ አይደለም። ይህን ኹሉ የሚንድ ስለ ኾነ፥ በወሬ ካልቀረ በቀር ሊደረግ የሚችለው ጥገናዊ ማሻሻያና ነቀፌታን ሊያስወግድ በሚችል መልኩ የማስተካከል ሥራ እንደሚኾን ይጠበቃል።
ገድላትን የማረም ሥራ የሚሠራ ከኾነ እነዚህ ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘት አለባቸው፦
የቀደሙ ድርሰቶችን (የአንዱን ድርሰት ሌላው) ማረም ምን ያኽል መብት ነው? ምን ያኽልስ ተገቢ ነው?
እንዲህ ያለ ተመክሮስ አለ ወይ? ደራሲዎቻቸው በወደዱት መንገድ የጻፏቸው ስለ ኾነ የአንድን ሰው ድርሰት ወይም የፈጠራ ሥራ መሔስ እንጂ ማረም እንዴት ይቻላል? ማረም ካለበትም ደራሲው ነው እንጂ ሌላው ሰው መኾን አለበት ወይ?
ከእምነት አንጻር ሊወሰድ የታሰበው ርምጃ ሥነ ጽሑፋዊና ታሪካዊ ሀብትነታቸውን አያጠፋም ወይ?
ከዚህ ይልቅ ከክርስትና ትምህርትና ሥርዐት ውጪ ተደርገው ከቤተ ክርስቲያን ወደ ሙዚየም ቢዛወሩና ጥናትና ምርምር ለሚያደርጉ ሰዎች አገልግሎት ቢሰጡ አይሻልም ወይ? ደግሞስ ገድላትንና ድርሳናትን ማስተካከል እና/ወይም ማረም ያስፈለገው ለምንድን ነው?
ገድላትንና ድርሳናትን እናስተካክላለን የተባለው፥ መጻሕፍቱ በዋናነት ከታሪክና ከሥነ ጽሑፍ ቅርስነት ይልቅ፥ የሃይማኖት አካል ኾነው እንዲቀጥሉ ከመፈለግ የመነጨ ነው። ይህ ከችግሩ አዙሪት የሚያወጣ አይደለም። ስለዚህ በእኔ እምነት ተኣምረ ማርያምን፣ ገድላትንና ድርሳናትን ከማስተካከል እና/ወይም ከማረም ይልቅ፥ ፕሮፌሰር ጌታቸው እንደ ሰጡት ምክረ ሐሳብ 1 እነርሱን ከእምነትነት ወደ ታሪክነት ማሻገሩ የተሻለ ነው። ይህም በአንድ ጊዜ ሳይኾን በቂ ጥናትና ዝግጅት አድርጎ ሊወሰድ የሚገባው ርምጃ መኾን አለበት። አሊያ ይደረጋል የተባለው ማስተካከያ እና/ወይም ዕርማት የድርሰቶቹን ሥነ ጽሑፋዊ ቅርስነትና ታሪካዊነት ያበላሻል። ጥገናዊ እንጂ ሥር ነቀል ለውጥም አያመጣም። ለጊዜው ነቀፌታን ሊያስወግድ ቢችል እንኳ ከመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርት ጋር በረቀቀ መንገድ መጋጨቱ አይቀርም።
Share this article:
A new report from a Catholic organization found that the persecution of Christians is worse “than at any time in history.
“የሰላም መረበሽና የፍትሕ ቀውስ እየከረረ በመጣበት በዚህ ዘመን፣ እንደ ክርስቲያን ተስፋ የምናደርገው የታሪክን አቅጣጫ በልጓም የያዘውን ልዑል እግዚአብሔርን ነው።” መጋቢ ግርማ በቀለ (ዶ/ር) “እግዚአብሔር አለ!” በተሰኘው በዚህ ዐጭር አጽናኝ መልእክት ያስተላለፉትን ያንብቡ።
አንዳንዶች ሰዎች በሕይወታቸው ትርጉም ላለው፣ ብሎም ዓላማቸው ላደረጉት ጉዳይ እስከ ሞት ሊደርስ በሚችል መከራ ውስጥ ያልፋሉ፡፡ ማዕበሉ የሚንጥና የሚያንገላታ ቢሆንም፣ የሕይወት ምስቅልቅሎሹ ቢበረታም ዓላማቸውን ግን የሙጥኝ ይላሉ፡፡ በእውነቱ እንደነዚህ ዐይነት ሰዎች ተፈትነው ያልተረቱና የማይናወጥ ጠንካራ ሰብዕናን የተላበሱ ናቸው፡፡
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment