
“የሁላችን ድርሻ ተጠራቅሞ ነው ውጤት ያመጣነው”
ዘላላም አበበ በኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስትያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማኅበር (ኢቫሱ) ውስጥ ለረጅም ዓመታት አገልግሏል፡፡ ለአራት ዓመታት በደቡብ አካባቢ የኢቫሱ ቢሮ በሙሉ ጊዜ አገልጋይነትና የአካባቢው ቢሮ አስተባባሪ በመሆንና ከ1996 ዓ.ም. እስከ 2007 ዓ.ም. ለዘጠኝ ዓመታት ደግሞ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ በመሆን አገልግሎ በቅርቡ በራሱ ፈቃድ የዋና ጸሐፊነት ሥራውን አስረክቧል። ወንድም ዘላለም በትምህርት ዝግጅቱ ከአዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ እርሻ ኮሌጅ በእርሻ ሥራ እንዲሁም ከኢቫንጄሊካል ቲዮሎጅካል ኮሌጅ የመጀመሪያ ዲግሪውን በነገረ መለኮት ያግኝቷል። ዘላለም በአሁኑ ሰዓት አሜርካን አገር በሚገኘው Gorden Conwell Theological Seminary በሥነ አመራር የድኅረ ምረቃ ትምህርት በመመላለስ እየተከታተለ ይገኛል፡፡ በኢቫሱ ውስጥ በነበረው አገልግሎቱና በተያያዙ ጉዳዮች አስናቀ እንድርያስ ከዘላለም አበበ ጋር ያደረገው ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
Add comment