
ከሰውዬው ጀርባ የቆመችው ታላቋ ሴት – ካትሪን ቫን ቦራ
የማርቲን ሉተር ባለቤት ስለነበረችው ካትሪን ቫን ቦራ የሚያወሳው ይህ ጽሑፍ፣ የሉተር የተሓድሶ እንቅስቃሴ ዳር እንዲደርስ ስላበረከተችው ጉልሕ አስተዋጽኦ ታምራት ያዕቆብ እንዲህ ያስነብበናል።
[the_ad_group id=”107″]
5 አልበሞች ለአድማጭ አድርሷል፤ ከእነ አረጋኸኝ ወራሽና ሌሎች ድምፃውያን ጋር የሠራቸው ስብስብ ሥራዎችም አሉት። “ደህና ሁኝ ልበልሽ በእንባ እየታጠብኩኝ”፣ “ምነው ቀዘቀዘ ፍቅራችን”፣ ከሥራዎቹ መካከል ጎልተው የሚጠቀሱት ናቸው። ሰሞኑን በታክሲ ሾፌርነት መታየቱ ተሰምቶ አነጋግረነዋል።
Originally posted at BBC Amharic
ተፈራ ነጋሽ፦ አሁን 13 ዓመት ጨርሼ 14 ዓመት ሊሞላኝ አንድ ወር ይቀረኛል።
ተፈራ ነጋሽ፡-የተለያየ ዓይነት አስተያየት ነበር። የሚደግፉ አሉ። እንደገና ደግሞ በዛው ብቀጥል የሚፈልጉና የራሳቸውን ሐሳብ የሚሰጡም አሉ። እንዲሁ ደግሞ የሚቃወሙም ነበሩ። ዞሮ ዞሮ ውሳኔው ግን የራስ ስለሆነና ሕይወት ስለሆነ፣ መንፈሳዊ ነገር አንተ ለራስህ የሚገለጥልህ ነገር ስለሆነ፣ አንተ የተሰማህን ወይንም ደግሞ የተገለጠልህን ነገር ነው የምትኖረው።
ተፈራ ነጋሽ፡- እውነቱን ለመናገር ከሆነ የውሳኔህ ሁኔታ ነው የሚወስነው። እኔ ስወስን ምንም ነገር ሳልጨብጥ አይደለም የወሰንኩት። የሆነ ነገር ገብቶኝ በትክክል መንፈሴ ላይ የተረዳሁት ነገር ስለነበረ፣ ያ የተረዳሁት ነገር ደግሞ ከአእምሮ በላይ የሆነ ትልቅ ስለሆነ፣ ከምንም ነገር ጋር አላነፃፅረውም። እና በቀጥታ ወደዚህ ወደ መንፈሳዊው ዓለም ስመጣ በፊት የነበሩኝ ልምዶች እንዴት እንደሆነ ሳላውቅ ከኔ ተለይተው ነው ያገኘኋቸው። እና ሙዚቃውም ዘፈኑም አብሮ ወዴት አንደሄደም አላውቅም። ፍላጎቱ ጠፍቷል። አሁን የድሮ ሥራዎቼን በምሰማበት ጊዜ እውነቱን ለመናገር ከሆነ ምንም ስሜት አይሰጠኝም።የኔ እስከማይመስሉኝ ድረስ ነው ውስጤ የተለወጠው ልልህ ፈልጌ ነው።
ተፈራ ነጋሽ፡- እውነት ነው፤ ምክንያቱም ወደ መጽሐፍ ቅዱስ ከሄድን ምን ይላል፣ “ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው” ይላል። አዲስ ፍጥረት የሚለው ነገር እውነት ነው። ወደዚህ አዲስ ማንነት ስመጣ ውስጤ ለውጥ ተካሄዷል። በዐይን የማይታይ ግን መለኮት የሚሠራው ውስጣዊ ለውጥ ተከስቷል። ያ ለውጥ ዘፈንን ብቻ አይደለም፤ ሌሎች ማንኛቸውንም ነገሮች በተለይ ኀጥያት ተኮር የሆኑ ነገሮች ወዴት እንደሄዱ አላወቅሁም።
ለምሳሌ አንድ ነገር ልንገርህ፤ ጫት እቅም፣ መጠጥም እጠጣ ነበር። ግን ይህንን ውሳኔ በወሰንኩ በማግሥቱ ዘጠኝ ሰዓት ላይ ነው ትዝ ያለኝ። ውስጤን ሳዳምጠው የለም። ልክ እንደዚህ ዘፈኑም አብሮ ሄዷል። ስለዚህ ይህ ውስጣዊ ለውጥ ነው፤ ይሄ የማንነት ለውጥ ነው።
ተፈራ ነጋሽ፡- እንደዛ አላስብም፤ ተቃውሞም አላሰማም። ምክንያቱም ሥራዎቹ የብቻዬ አይደሉም። የሙዚቃ ባንዱ፣ ገጣሚያን፣ ዜማ ደራሲያን አሉ። ብቻዬን የሠራሁት ሥራ ስላልሆነ እነኛም ሰዎች መብት አላቸው። ሌላው ቢሰሙም ላለፈው ነገር እኔ አልጠየቅም። የዛን ጊዜ ትክክል ነበርኩ፤ አሁን ደግሞ የበለጠ ትክክል ነኝ። በዛን ወቅት ጥፋት አጥፍቼ ቢሆን አሁን በምሕረት ወጥቼያለሁኝና ያንን ነገር እግዚአብሔር ረስቶልኛል። ወደ ኋላ ተመልሼ ይህ ለምን ሆነ? ለምን ዘፈንኩ? ብዬ አልፀፀትም። በሌላ መንገድ ካየነው ሥራዎቹ ሲሰሙ አንድም ሰዎች መነጋገሪያ ሊያደርጉትና ሰዎች ራሳቸውን ውሳኔ መምረጫ እንዲያደርጉት መንገድ ሊፈጥር ስለሚችል ለምን የኔ ሥራ ተከፈተ፣ በሚዲያ ላይ መደመጥ የለበትም የሚል አቋም የለኝም።
ተፈራ ነጋሽ፡- ከዛ በፊትም የተለያየ ሥራ እሠራ ነበር። ለመኖር መሥራት አለብኝ። አሁን ራይድ ሲመጣ መኪናው እጄ ላይ ስላለ በቀጥታ ሰሌዳውን ወደ 3 ቁጥር አዙሬ፣ የንግድ ፍቃድ አውጥቼ፣ ከድርጅቱ ጋር ተስማምቼ መስራት ጀምሬያለሁ። ሥራው ጥሩ ነው። በጣም ተመችቶኛል። ይህንን ውሳኔ የወሰንኩበት ምክንያት ደግሞ ምንም አይነት ሥራ ስትሠራ በቀዳሚነት የአእምሮ እረፍት ታገኛለህ። ሌላው ደግሞ የሚያስፈልግህን ነገር ታሟላለህ። ሌላ ሰውንም የምትደግፍበት የምታግዝበት አቅም ታገኛለህ። ለመንግሥትም ግብር ትከፍላለህ። ስለዚህ ይህንን ሥራ ሳገኝ ምንም አላቅማማሁም፤ አላመቻመችኩም።
ተፈራ ነጋሽ፡- የሚመዘግቡት ልጆች የሚያውቁኝ አይመስለኝም። ያን ጊዜ የነበረኝን የታዋቂነት መንፈስ ትቼዋለሁ። ነገር ግን የራይድ ሥራ አስኪያጅ ስታገኘኝ ደስ የሚል ነገር አይቼባታለሁ። ጥሩ አድርጋ አስተናግዳኛለች። እኔ ራሴን እንደ ማንኛውም ተራ ሰው ነው የምቆጥረው። የድሮው ስሜት የለኝም።
ተፈራ ነጋሽ፡- እስካሁን በጎ ምላሽ ነው ያለው። አንዳንድ ከልብ አድናቂዎች ደንገጥ የማለት ነገር ታይባቸዋለህ። ብዙ ሰዎች ውሳኔዬን ያከብራሉ ያደንቃሉም። ምክንያቱም የተሻለ እንደሆነ ያስታውቃል። እንዴት ያስታውቃል ካልከኝ ዝም ብለህ ሰውን ፊቱን ስታየው ሰላሙን ታይበታለህ። እኔ ደግሞ አሁን ያለኝ አቋም ከዕድሜዬ ጋር እንኳ አይገናኝም። 56 ዓመቴ ነው ግን የ40 ዓመት ጎልማሳ ነው የምመስለው። እንደውም አንዳንድ ሰዎች ‘እሸት መሰልክ’፣ ‘ገለፈፍክ’፣ ‘ለመለምክ’ የሚሉኝ አሉ። በውስጤ የሚታየው ሰላም ፊቴ ላይ ስለሚታይ፣ ከማንም ጋር የመግባባቱን ፀጋ ደግሞ እግዚአብሔር ስለሰጠኝ፣ ከብዙ ሰዎች ጋር እናወራለን። የሚፈልጉትን ይጠይቁኛል፤ እኔም እንደሚገባው ከዚህኛውም ከዛኛውም እያጣቀስኩ መልስ እሰጣቸዋለሁ።
ተፈራ ነጋሽ፡- ደስ እንዳላቸው የሚነግሩኝ አሉ። እንደውም ስልኬን ወስደው እንደዘመድ የምንጠያየቅም አሉ። ከጀመርኩ ሦስት ወር ከአስራ አምስት ቀን ቢሆነኝም በዚህ አጭር ጊዜ በርካታ ሰው አግኝቻለሁ። የተለያየ ዕውቀት፣ ልምድ ያላቸው ሰዎች አግኝቻለሁና በጣም ደስ ይላል።
ተፈራ ነጋሽ፡- ወድጄዋለሁ። ጭቅጭቅ የለውም። ድካም የለውም። ሥራው አንተ ያለህበት ድረስ ነው የሚመጣልህ። የምታገኛቸው ሰዎችም አሪፎች ናቸው። ወድጄዋለሁ።
ተፈራ ነጋሽ፡- የኮሚሽን ሥራዎችን ሞክሬያለሁ። ቤት ሠርቶ ለመሸጥም ሞክሬያለሁ።
ተፈራ ነጋሽ፡- አዎ። ግን አጭር ጊዜ ነው የሠራሁት። መሬት ስለነበረኝ ቤት ሠርቼ ነው የሸጥኩት፤ እሱ ሁለት ሦስት ነገር ወጣው። አሁን ሌላ ቤት ጀምሬ ቆሟል። ያው የሕንፃ መሣሪያ ውድነት አለ፤ በዚህ ሰዓት ላይ። እሱ ሥራ ውስጥ ለመግባት ሐሳብ አለኝ። ሌላው ደግሞ አገልግሎት ላይ ነኝ። በነገራችን ላይ ሙዚቃውን አልተውኩም። የመንፈሳዊ ሙዚቃ ላይ በዝማሬ አገለግላለሁ።
ተፈራ ነጋሽ፡- እኔ ይህኛውን አባባል አልደግፈውም። ይህንን ሥራ እኔ የምሠራው ምንም ነገር አጥቼ አይደለም። በቤተ እምነት ውስጥ አገልግሎት አገለግላለሁ፤ እርሱ ለኑሮ አያንስም። በዛ ላይ የሚከራይ ቤትም አለኝ። አሁን በጣም ድሃ የመሆን ጉዳይ ሳይሆን ወደ ዚህ ያመጣኝ የጊዜ መኖር ጉዳይ ነው። እኔ የማገለግለው በሰንበት ወይንም በአዘቦት ቀናት ማታ ማታ ነው። ስለዚህ ቀን ቀን በከንቱ የሚያልፈውን ጊዜ ብጠቀምበት ጥሩ ነው። በተጨማሪም ሰው አገኝበታለሁ፤ ከዚህ ሁሉ ባሻገር ደግሞ ገንዘብ አገኝበታለሁ። የሚገኝበት ገንዘብ ቀላል አይደለም። በወር ውስጥ 30 ሺህ ሊያገኝ የሚችል ብዙ ሰው አለ ብዬ አላምንም። ከዚህ ሥራ በቀን ከሺህ ብር በላይ ታገኝበታለህ። እና ገቢው ራሱ በጣም ዝቅተኛ የሚባል አይደለም። እና ትልቁ ነገር ጤና ኖሮህ ሠርተህ የምታገኘው ነገር ነው። ይህንን ነገር እንድሠራ ያደረገኝ የዝቅታና የከፍታ ነገር አይደለም። እግዚአብሔር ይመስገን በከፍታ ውስጥ ነኝ፤ ከክርስቶስ ጋር።
ተፈራ ነጋሽ፡- ሐዋሪያው ጳውሎስን ታውቀዋለህ?… እነ ጴጥሮስን ታውቃቸዋለህ?… አልተመለሱም ።ለምን እንዳልተመለሱ ታውቃለህ? …ያዩት ምድራዊ ነገር አይደለም። ሰማያዊ ነገር ነው ያዩት።… ታንክ ቢመጣ ወደኋላ አልመለስም። ወደኋላ ከምመለስ ሞት ይሻለኛል።
Originally posted at BBC Amharic
Share this article:
የማርቲን ሉተር ባለቤት ስለነበረችው ካትሪን ቫን ቦራ የሚያወሳው ይህ ጽሑፍ፣ የሉተር የተሓድሶ እንቅስቃሴ ዳር እንዲደርስ ስላበረከተችው ጉልሕ አስተዋጽኦ ታምራት ያዕቆብ እንዲህ ያስነብበናል።
Like Christmas itself, we can become nostalgic about reconciliation rather than embrace the messy grace and humility that it requires.
ከተራዛሚ ግጭቶችና ቍርቍሶች ለመውጣት ብዙ አገሮች ድኅረ ግጭት የሰላም ግንባታ ትግሎችን አካሂደዋል፤ እያካሄዱም ይገኛሉ። ማኅበረ ሰብ ፊትና ጀርባ ሆኖ ከቆየባቸው የተራዘሙ ግጭቶች ወጥቶ፣ አንዲትን በራእይ የተጣጣመች አገር መልሶ መገንባት “መደመር” ከሚለው ቃል ጋር ሳይጋጭ፣ ነገር ግን ከዚያ በዘለለ መልኩ በርካታ የሰላም ግንባታ ሒደት ያለበት ውስብስብና ተከታታይ ተግባራትን ይጠይቃል።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment