
ልዩ ወንጌል
በሕንጸት ቁጥር 1 ዕትም፣ በአውራ ነገር ዐምድ ሥር “የወንጌላውያኑ መንታ መንገድ” በሚል ሐተታዊ ጽሑፍ ተስተናግዶ ነበር፡፡ ጽሑፉ በዋናነት ከመቶ ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የወንጌላውያን ክርስትና በኢትዮጵያ ይዟቸው ስለመጣው ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ለውጦች በማተት፣ አማኝ ማኅበረ ሰቡ ስላበረከታቸው በጎ አስተዋጽዖዎች በመጠቆም ላይ ያተኮረ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ይህንን በጎ ተጽእኖውን ማስቀጠል በማይችልበት ደረጃ ላይ እንደደረሰና ለዚህም ምክንያቱ ልዩ የሆነ አስተምህሯዊ አቋምና ልምምድ በቤተ ክርስቲያን መተዋወቁ እንደ ሆነ ይጠቁማል፡፡ ይህ ልዩ አስተምህሮና ልምምድ ደግሞ በ“እምነት እንቅስቃሴ” ወይም በ“ብልጽግና ወንጌል” የተጠመቀ “ክርስትና” ወደ አማኝ ማኅበረ ሰቡ መዝለቁ ነው፡፡
Add comment