
እውነተኛ አገልጋይ ማነው?
የምንኖረው እጅግ በዘመነ ትውልድ ውስጥ ነው። በዘመኑ ውስጥ በዓይናችን የምናያቸውና በልቡናችን የምናስተውላቸው በርካታ ነገሮች አሉ። በተለይም በብዙ አቅጣጫ ውሸተኞች ሆነው ሳሉ ነገር ግን እውነተኛውን መስለው የሚገለጡ ነገሮችን እናስተውላለን።
[the_ad_group id=”107″]
በዚህ ዓለም በታወከችበት የCOVID-19 ወረርሽኝ ጤና ቀውስ፣ እንደ ክርስቲያን ተስፋ የምናደርገው ልዑል እግዚአብሔርን ነው። እርሱ በፈጣሪነቱ፣ ፍጥረትን ሁሉ፣ የሚታየውንና የማይታየውን ሁሉ በሥልጣኑ ቃል ደግፎ ይዟል። ዓለም በእርሱ ሉዓላዊነት ውስጥ እንጂ፣ በነገሥታትና ዐዋቂዎች እጅ አይደለችም። የእኛንም ሆነ የዓለምን ታሪክ በልጓም የያዘን ጌታ ነው የምናመልከው። እርሱ በመገረምም ሆነ በድንጋጤ አይያዝም፤ ነገንም በሥጋት ወይም በተስፋ አይጠብቅም! በማንም አይደገፍም፤ ለሥራውና ውሳኔው ትክክለኛነት ማንንም አያስፈቅድም፤ ማስተዋሉ ፍጹም ስለ ሆነ፣ ምክርም ከማንም አይጠይቅም፤ ዕውቀት አይጨመርለትም፤ አልገባኝም አሰረዱኝ አይልም፤ ነገሮች ሳይጀመሩ ፍጻሜያቸውን ያውቃልና!
ታዲያ በዚህ አምላክ ልባችን ካላረፈ፣ በማን ያርፋል? “ዕረፉ” የሚለው የዕብራይስጥ ቃል “ራፋኽ (רפה – râphâh) የሚያሳያን፣ ራስን ሙሉ ለሙሉ ለእግዚአብሔር ሁሉን ገዢነት አሳልፎ መስጠት፣ በእርሱ ላይ መውደቅ፣ የትም ከማያደርስ አድካሚ የራስ ጥረት ከመባከን፣ ሙሉ በሙሉ በእርሱ ላይ መደገፍ፣ መልስ የሌለውን የጊዜውን ጥያቄ ለእርሱ መተው፣ መውጫ የሌለው የሚመስለውን የጊዜውን የመከራ ሽክርክሪት ከመታገል ይልቅ፣ “እግዚአብሔር መውጫ አለው” ብሎ ማረፍ፣ ከእጃችን ወጥቷል፣ አብቅቶለታል ያልነውን ጉዳይ ከመጨነቅ ይልቅ፣ ከልዑሉ ዐይኖች አልተሰወሩም ብሎ በእርሱ ላይ ጥሎ ማረፍ … በአጠቃላይ ሕይወትን ሁሉ በእርሱ፣ “በታላቁ እኔ – THE GREAT I AM” ላይ ማሳረፍን ያመለክታል!
በዚህ ዓለም ዐቀፍ የጤና መታወክና የመኖር ዋስትና በተናጋበት ወቅት፦
የሃይድልበርግ የሃይማኖት ማስተማርያ መግቢያውን ልተውላችሁ፦
That I am not my own,
but belong with body and soul,
both in life and in death,
to my faithful Saviour Jesus Christ.
(Heidelberg Catechism)
ጌታ እግዚአብሔር በያለንበት፣ አገራችንንም በምሕረቱና በጥበቃው ይሸፍን፤ የተጎዱ አገራትንም ያስብ። አሜን!
Share this article:
የምንኖረው እጅግ በዘመነ ትውልድ ውስጥ ነው። በዘመኑ ውስጥ በዓይናችን የምናያቸውና በልቡናችን የምናስተውላቸው በርካታ ነገሮች አሉ። በተለይም በብዙ አቅጣጫ ውሸተኞች ሆነው ሳሉ ነገር ግን እውነተኛውን መስለው የሚገለጡ ነገሮችን እናስተውላለን።
“በሰማይ ከአንተ በቀር ማን አለኝ? በምድርስ አንተን ካገኘሁ ምን እሻለሁ?” (መዝ. 73፥25)
Proactively deploy backward-compatible catalysts for change rather than maintainable channels. Seamlessly create cost effective infrastructures via frictionless process improvements. Phosfluorescently target effective convergence vis-a-vis mission-critical
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment