
ድንቅ እና ታምራት ለምን?
አማረ ታቦር በዚህ ጽሑፉ፣ በብሉይ እና በአዲስ ኪዳናት የተደረጉት ድንቆችና ታምራት በዘመን የሚከፈሉ መሆናቸውን በማመልከት፣ ለምን ዐላማ ይደረጉ እንደ ነበረ ያወሳል። በዚህ የመጀመሪያ ክፍል፣ በብሉይ ኪዳን የተደረጉትን ታምራትና ድንቆች በዘመን ሰፍሮ ያስቃኛል።
[the_ad_group id=”107″]
“ሜሲን ልንሸጥላችሁ ዐስበናል”
“ምን አላችሁ እና ነው የምትሸጡልን፤ አንድ ያላችሁ እሱ”
“እናንተም ይህን አላችሁ?! ሲጀመር ዋጋውን ከቻላችሁት እኮ ነው”
የታክሲው ረዳት እና ሹፌሩ የጀመሩትን ጨዋታ አንድ ሁለት የሚሆኑት ተሳፋሪዎች ተቀላቀሉበት:: “እንሸጣለን”፣ “አንገዛም” … በውስጤ ʻከት ብለሽ ሳቂʼ የሚል ስሜት ተፈጠረብኝ:: ምን እንደሚሸጥ እና እንደሚለወጥ ለእርሶ መንገር ተገቢም አይመስለኝ:: ስለ ስፔን እና እንግሊዝ ክለቦች እያወሩ ነው ብዬ ማለት ጋዜጦቻችንን፣ ሬዲዮ እና ቴሌቪዥኖቻችንን ማስናቅ ነው:: እኔን ያሳቀኝ ግን እነሱ ሻጭ እነሱ ገዢ ሆነው መከረከራቸው ነበር:: “የእኛ” የሚለው የቡድን ስሜት የፈጠረው ነገር …፡፡
የቡድን ስሜት ወይም ደጋፊነት እጅግ እየበረታ በመጣ መጠን “እኔ” የሚለው ሐሳብ ይወጣና እኛ ውስጥ ራስን ማግኘት ይመጣል:: “እኔ”ን ረስቶ “እኛ” ብቻ ብሎ መኖር ይቻላል ግን?
ዛሬ የቡድን ስሜት እንዲህ በርትቶ መታየት የጀመረው በኳስ ደጋፊነት ብቻ አይደለም፤ እርስዎ ሌላም ቦታ ያገኙት ይሆናል፡፡ የእኔን ግን ላጨውትዎ:: ቃሉ “ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ መልካም ነው” ስለሚል ኅብረት መሥርተናል፤ በክርስቶስ ኢየሱስ አዳኝነት አምነናል የምንልም ተሰባስበናል:: ይህንን ስብስብ ግን ሲያስፈልግ እንደ ብሔራዊ ቡድን ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት፣ ሲያስፈልግ ደግሞ እንደ ክለብ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ስንደግፈው እና በቡድን ስሜት ስንጮኾለት የምንገኝበት ጊዜ ብዙ ነው::
ጥቂት ሐሳብ ይዘው ቡድን የተቀላቀሉ፣ ብዙ ሐሰብ ባለው በብልሁ ሳይሆን በብልጡ ይበለጣሉ::
በቡድን መጮኽ ከፍ ያለ ድምፅ እንዲወጣ ያግዛል:: በቡድን ማሰብ ለራስ ሐሳብ ስንፍና ይመቻል:: የቡድን ደጋፊ መሆን ደግሞ በቡድን የመመካትን ስሜት ይፈጥራል:: ይህ ደግሞ የቡድንን ሥራ ሳይሆን ቡድንን ራሱ በቡድንነቱ ብቻ ፍጹም አድርጎ ማየትን ያስከትላል:: በቡድን እና በቡድን ደጋፊነት ሳቢያ ተፈጥረው ካየኋቸው እንከኖች መካከል የቅርብ ሰሞን ገጠመኜን ከመንገሬ በፊት ለእርስዎ አንድ ጥያቄ ላቅርብልዎ:: ሰዎች በኢየሱስ አምነው ከጥፋት በተመለሱና ከሲኦል በዳኑ ጊዜ በሰማይ ደስታ እንደ ሆነ ቃሉ ነግሮናል:: እንደው ግን “በተለይ እነ እከሌ እና መሰሎቻቸው ሲድኑ የበለጠ ደስታ ይሆናል” ተብሎ ተጽፍዋል እንዴ? ልክ የእከሌ ቡድን ደጋፊ እንደሚከራከረው የተጨዋች ግዢ ዐይነት ግርግር እያየሁ ስለሆነ እኮ ነው ይህን መጠየቄ::
አሁን ወደ ሰሞኑ ገጠመኜ ልመለስ:: መገናኛ ብዙኀን እና ማኅበራዊ ድረ ገጽ ብድግ ቁጭ እያደረጉት ያለው የሰሞኑ ወሬ ነው:: ʻእከሌ የተበለው ዘፋኝ የእንትን ሃይማኖት ተከታይ ሆነ፤ እከሊትም ጭምርʼ:: ታዲያ፣ ክርክሩ ጦፎ ባየሁበት ወቅት ነበርና ይህንን የታክሲ ላይ ጨዋታ የሰማሁት፣ ለራሴ የነገርኩትን ለእርስዎም ብነግርዎ ብዬ ነው:: ምንም እንኳን በነጻ ብናገኘውም በሕይወት ዋጋ ግን ተገዝተናል:: የተገዛነው ግን በእኩል የሕይወት ዋጋ ነው፤ የአንዳችን ዋጋ ከአንዳችን ዋጋ አይበልጥም:: ስለዚህም፣ እንደ ቡድን ደጋፊዎች በመሆን “ተጨዋች የመግዛት” ጨረታ ውስጥ ባንገባስ:: አይመስልዎትም?
Share this article:
አማረ ታቦር በዚህ ጽሑፉ፣ በብሉይ እና በአዲስ ኪዳናት የተደረጉት ድንቆችና ታምራት በዘመን የሚከፈሉ መሆናቸውን በማመልከት፣ ለምን ዐላማ ይደረጉ እንደ ነበረ ያወሳል። በዚህ የመጀመሪያ ክፍል፣ በብሉይ ኪዳን የተደረጉትን ታምራትና ድንቆች በዘመን ሰፍሮ ያስቃኛል።
በዚህ ልዩ ዕትም፣ ጋዜጠኛና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች የሆነው እስክንድር ነጋ የሕንጸት ዕንግዳ ሆኖ ቀርቧል። አገራችን ኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶችና ዴሞክራሲ የሚከበሩባት አገር እንድትሆን መሥዋዕትነትን የጠየቀ ትግል አድርገዋል ከሚባሉት ግለ ሰቦች መካከል አንዱ እስክንድር ነው። በዚህም፥ ከዘጠኝ ጊዜያት በላይ ደጋግሞ ለእስር የተዳረገው እስክንድር፣ በአጠቃላይ ከዘጠኝ ዓመታት በላይ በእስር አሳልፏል።
በባለፈው የፈረንጆች ዓመት ማብቂያ ላይ፣ ማለትም እ.ኤ.አ. ዲሴምበር 25 2014 ኤሪክ ሜታክስስ የተባለው ዕውቅ ጸሐፊ በዎልስትሪት ጆርናል “Science Increasingly Makes the Case for God” በሚል ርእስ ሳይንስ ፈጣሪ ስለ መኖሩ የሚቀርቡ ሙግቶችን ዕለት ዕለት ይበልጥ እየደገፈ ስለ መምጣቱ ጽፏል።1 ይህ አነጋጋሪ ጽሑፍ እ.ኤ.አ. በ1966 በታይም መጽሔት “ፈጣሪ ሞቷል?” የተሰኘውን ጽሑፍ መነሻ በማድረግ የዘመኑ ሳይንስ የፈጣሪን አለመሞት፣ ብሎም ስለ መኖሩ ይበልጥ ርግጠኛነትን የሚያስጨብጥ ግኝት ላይ እንደ ደረሰ ይናገራል። ይህ ግኝት ምን እንደሆነና ከሜታክስስ ጽሑፍ ጋር የተገናኙ አንዳንድ ሐሳቦችን በዛሬው ጽሑፋችን ለመዳሰስ እንሞክራለን።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment