
ጤነኛ ቤተ ክርስቲያን እንዲኖረን ኀላፊነታችንን እንወጣ
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስትና ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በፈተና ውስጥ እንዳለ እናምናለን፡፡ እነዚህ ፈተናዎች ደግሞ የወንጌላውያኑን ማንነት እያደበዘዙ፣ በማኅበረ ሰቡ ዘንድ ያለውን ተቀባይነት እያጠፉ፣ የአማኞችን የሕይወት ጥራት እየቀነሱ፣ ቤተ ክርስቲያን ምድራዊና ራስ ተኮር ብቻ እንድትሆን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ይህ በዚህ ከቀጠለ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ምን ዐይነት መልክ ሊኖረን እንደሚችል መገመት አስቸጋሪ አይሆንም፡፡
Add comment