[the_ad_group id=”107″]

ለማነጽ እንሠራለን!

ሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር፣ ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስና ስለ ወንጌሉ እውነት እንዲሁም እርሱ ስለ መሠረታት ቤተ ክርስቲያን ግድ የሚላቸው ሰዎች ተሰባስበው ያቋቋሙት መንፈሳዊ ማኅበር ነው፡፡ ማኅበሩ በምድራችን ላይ ያለችው ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን፣ ክርስቶስን መስላ እንድታድግ በሚደረገው የማነጽ ሂደት ውስጥ የበኩሉን ድርሻ ለመወጣት ያለመ ነው፡፡ ስያሜውም ይህንኑ የሚገልጽ ነው፤ “ሕንጸት” የግዕዝ ቃል ሲሆን፣ “ማነጽ” ወይም “መገንባት” የሚለውን ፍቺ ይይዛል፡፡

ሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር በተግባራቱ በኩል ተፈጽሞ ማየት የሚፈልገው ራእይ አለው፤ ይህም፡- “የወንጌላዊያን ክርስቲያን ማኅበረ ሰብ መጽሐፍ ቅዱሳዊ በሆነ ክርስቲያናዊ አስተምህሮ እና ሥነ ምግባር ላይ ታንጾ፣ የወንጌል ተልእኮውን ሲወጣ ማየት፡፡” የሚል ነው፡፡

ሕንጸት መጽሔት ማኅበሩ ራእዩን ለማሳካት ከሚጠቀምባቸው መንገዶች አንዱ ነው፡፡ ሕንጸት መጽሔት በይዘትም ሆነ በቅርጽ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል፡፡ ይህንን ስንል ሥራችን እንከን አልባ ነው ማለታችን አይደለም፤ ይልቁን በተሻለ ደረጃ ለማገልገል ብዙ እንደሚቀረን እናምናለን፡፡ የመጽሔቱ ስያሜ እንደሚጠቁመው፣ የክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን ለማነጽ ብቻ እግዚአብሔር የሰጠንን ጉልበትና ጊዜ እንደምንጠቀም ተስፋ እናደርጋለን፡፡

ማኅበሩ እውን እንዲሆን በርካታ ሰዎችና ተቋማት ዐይነቱ የተለያየ ድጋፍ አድርገዋል፡፡ ልንሠራ ያሰብነውን በነገርናቸው ጊዜ በራእያችን በማመን አብሮነታቸውን የገለጹልንንና ሐሳባቸውን፣ ገንዘባቸውን፣ ጊዜያቸውንና ጉልበታቸውን የሰጡንን ወገኖቻችንን ልናመሰግን እንወዳለን፡፡

ለሕንጸት አንባቢያንን በአጠቃላይ የምንለው ቢኖር፣ የምንጽፈውን በማንበብ ሐሳባችሁንና አስተያየታችሁን እንድታካፍሉን በአክብሮት እየጠየቅን፣ እውነት ያለበትን፣ ቅንነት የሞላበትንና ለእግዚአብሔርና ለመንግሥቱ የሚሆነውን ምክር ሁሉ እንደምንሰማ ርግጠኞች በመሆን ነው፡፡ እናገለግለው ዘንድ ዕድል የሰጠን እግዚአብሔር ይመስገን!

ጤነኛ ቤተ ክርስቲያን እንዲኖረን ኀላፊነታችንን እንወጣ

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስትና ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በፈተና ውስጥ እንዳለ እናምናለን፡፡ እነዚህ ፈተናዎች ደግሞ የወንጌላውያኑን ማንነት እያደበዘዙ፣ በማኅበረ ሰቡ ዘንድ ያለውን ተቀባይነት እያጠፉ፣ የአማኞችን የሕይወት ጥራት እየቀነሱ፣ ቤተ ክርስቲያን ምድራዊና ራስ ተኮር ብቻ እንድትሆን እያደረጉ ይገኛሉ፡፡ ይህ በዚህ ከቀጠለ ከተወሰኑ ዓመታት በኋላ ምን ዐይነት መልክ ሊኖረን እንደሚችል መገመት አስቸጋሪ አይሆንም፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ

“የክርስቲያን ሚዲያዎች ሲታዩና ተግባራቸው ሲገመገምም አብዛኛዎቹ አንባቢውንም ሆነ ተመልካቹን የማይመጥኑ…ሆነው እናገኛቸዋለን” – ቃለ መጠይቅ ከዶ/ር ንጉሤ ተፈራ ጋር

ሚክያስ በላይ ከዶ/ር ንጉሤ ተፈራ ጋር ባደረገው ቆይታ፣ አማኝ ማኅበረ ሰቡን በሚመለከት ስለ ኮሙኒኬሽንና የመገናኛ ብዙኅን አጠቃቀም፣ አብያተ ክርስቲያናት ከኅብረተ ሰቡ ጋር ስላላቸው መስተጋብር እንዲሁም በአጠቃላይ ከቤተ ክርስቲያንን አመራር ጋር ሊያያዙ በሚችሉ ጭብጦች ዙሪያ ያደረገው ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው ቀርቧል።

ተጨማሪ ያንብቡ

ስለ ዘፈን

ዘሪቱ ከበደ በሕንጸት ድረ ገጽ ላይ ለንባብ ባቀረበችው በዚህ ጽሑፍ፣ በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አማኞች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኖ እስከ አሁን በዘለቀው የዘፈን ጕዳይ ላይ ብያኔዋን ትሰጣለች። “ይህን ጕዳይ ሳነሣ ለዘፈን ጥብቅና ልቈም ፈልጌ አይደለም። ይሁን እንጂ፣ እውነትን መናገርም ሆነ መነጋገር አስፈላጊ እንደ ሆነ ደግሞ አምናለሁ።” የምትለው ዘሪቱ፣ ወደ ጌታ የመጣችበትን ሂደትና የተለማመደችውን መንፈሳዊ ሕይወት እያስቃኘች፣ አማኝ ማኅበረ ሰቡ በርእሰ ጕዳዩ ላይ ሊኖረው ስለሚገባ ግንዛቤ ዐሳቧን ታካፍላለች፤ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ናቸው ያለቻቸው ማስረጃዎቿንም ታቀርባለች። በዚህ ብቻ አታበቃም፤ በሙዚቃ ጥበብ ውስጥ መዝለቅ የሚሹ ክርስቲያን ወገኖች ሊኖራቸው ስለሚገባ መንፈሳዊ አመለካከትና መውሰድ ስለሚጠበቅባቸው ጥንቃቄ የምክር ቃል ታካፍላለች።

ተጨማሪ ያንብቡ

Add comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.