
መሪነትም እንደ ውበት
ለመሆኑ፣ የየቤተ ክርስቲያኑ መሪዎች አንድን የአመራር ዘይቤ በሚመሯት ቤተ ክርስቲያን በሥራ ላይ እንዲውል ካደረጉ በኋላ በተለያዩ ምክንያቶች እንዳሰቡት የአመራር ዘይቤውን ውጤታማነት ማየት ቢቸግራቸው ምን ማድረግ ይችላሉ?
[the_ad_group id=”107″]
የወንጌል አማኝ ነኝ። የወንጌል አማኝ በመሆኔ ከክፉ ዳንኩ እንጂ ከዓለም አልወጣሁም። ከዓለም ወጥቼም ከሆነ፣ የወጣሁት ዓለማዊነት ከውስጤ ወጥቶ የወንጌል መልእክተኛ ሆኜ ወደ ዓለም እንድላክ እንጂ፣ የራሴን እና የብጤዎቼን ደሴት ሠርቼ፣ ተነጥዬ እንድኖር አይደለም። ጥበብ እንደ ጎደላት ሰጎን ጭንቅላቴን አሸዋ ውስጥ ቀብሬ ‘የለሁም’ ካላልኩ በስተቀር የአገሬ፣ የምድሬ ነገር ያገባኛል። ጥሪዬ ለምድር ጨውነት፣ ለዓለም ብርሃንነት እስከ ሆነ ድረስ ምድሩና ዓለሙ የሥራ መስኬ፣ የተግባር መከወኛዬ እንጂ ጥዬ የምሸሸው ጣጣ አይደለም። ያመንኩት የዓለምን መድኃኒት ነው፤ መድኃኒቱን ተቀብዬ መዳን ብቻ ሳይሆን መድኃኒት እንድሆን ተጠርቻለሁ። ስለዚህ ጥል ባለበት ፍቅርን፣ መለያየት ባለበት አንድነትን፣ ጥፋት ባለበት ልማትን፣ ኹከት ባለበት ሰላምን ለማወጅ ተጠርቻለሁ።
ሁላችንም እንደምናውቀው አገራችን ኢትዮጵያ በለውጥ ሂደት ላይ ትገኛለች። ይህ ለውጥ ትልቅ ተስፋ አንግቦ፣ በሥጋቶች ታጅቦ እየተመመ ነው። ትናንት አሸባሪ ተብለው በባዕድ ምድር ይንቀሳቀሱ የነበሩ የፖለቲካ ኀይሎች ዛሬ በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ወደ አገር ቤት ገብተዋል። ተዘግተው የነበሩ መገናኛ ብዙኀን ተከፋፍተዋል። ፌስ ቡክ፣ ዩቲዩብ እና የተለያዩ ማኅበራዊ የመገናኛ ዘዴዎች እያንዳንዱን ግለ ሰብ ጋዜጠኛ፣ እያንዳንዱን ገጽ ጋዜጣ አድርገውታል። ላለፉት 44 ዓመታት የተቀነቀነው የሶሻሊዝም አስተሳሰብና ላለፉት 27 ዓመታት የናኘው ዘር ተኮር አስተሳሰብ ገና ከአገራችን ጫንቃ ላይ አልተራገፈም። ከዚህም የተነሣ እዚህም እዚያም የሕይወት፣ የአካልና የንብረት ጥፋቶች ይሰማሉ። ታዲያ እንደ ወንጌል አማኝ በእንዲህ ዐይነት ሁኔታ ውስጥ ‘ምን ላስብ? ምንስ ላድርግ?’ የሚል ጥያቄ መነሣቱ አይቀርም። ሐሳቤን የምሰነዝረው የትኛውንም ቡድን በመደገፍ ወይም በመንቀፍ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ አንድነቷ ተጠብቆ፣ ሰላሟ ደምቆ፣ ልማቷ አሸብርቆ ለማየት ካለኝ ናፍቅቶ በመነሣት ብቻ ነው። ለጊዜው ሦስት ምክሮችን ልለግሥ።
“ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን ባርኪ፥ ምስጋናውንም ሁሉ አትርሺ” መዝ. 103፥2
ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ወደ ሥልጣን ከመጡበት መጋቢት 24፣ 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ያሳለፍናቸው 136 ቀናት (ይህ ጽሑፍ እስከተጻፈበት) በአገራችን ታሪክ የተለዩ ጊዜያት ናቸው ቢባል ማጋነነ አይሆንም። በእነዚህ ጊዜያት እግዚአብሔር ከአእምሮ በላይ የሆኑ ታላላቅ ነገሮችን አድርጎልናል። ስለዚህ በዕለት ተዕለት ዜና ከመወሰዳችን በፊት፣ ቆም ብለን ወደ ኋላ ተመልክተን፣ ባርኮታችንን እየቆጠርን እግዚአብሔርን ልናመሰግን ይገባናል።
“ዐውሎንም ጸጥ አደረገ፥ ሞገዱም ዝም አለ። ዝም ብሏልና ደስ አላቸው፤ ወደ ፈለጉትም ወደብ መራቸው። ለሰው ልጆች ስላደረገው ተአምራት ስለ ምሕረቱም እግዚአብሔርን አመስግኑ።” መዝ. 107፥29-31
Share this article:
ለመሆኑ፣ የየቤተ ክርስቲያኑ መሪዎች አንድን የአመራር ዘይቤ በሚመሯት ቤተ ክርስቲያን በሥራ ላይ እንዲውል ካደረጉ በኋላ በተለያዩ ምክንያቶች እንዳሰቡት የአመራር ዘይቤውን ውጤታማነት ማየት ቢቸግራቸው ምን ማድረግ ይችላሉ?
በቤተ ክርስቲያንና በመንግሥት መካከል ያለውን ግንኙነት በሚመለከት በታሪክ ሁለት ጽንፎች መንጸባረቃቸውን የሚያስታውሰው ዶ/ር ግርማ በቀለ፣ ቤተ ክርስቲያን በአሁኑ ጊዜ በአገራችን የሚታየውን እኩይ ምግባር በአደባባይ ለመኮነን አቅም ሊያንሳት አይገባም ይላል።
In the following article, titled: “Does PM Abiy’s religion matter?” Naol Befekadu argues it does matter. Here is why.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment