
“አትብሉ – ብሉ”
በዔድን የነበረው ሕይወት “መልካም” እጅግ ያማረም ነበር። ከምድር ዐፈር የተበጀው ሰው በዚህ ውብ ስፍራ ተቀመጠ፤ እንዲኖር፣ እንዲያለማ፣ እንዲንከባከብም። በዚያ የነበረው ዛፍ ሁሉ “የሚያስደስት ለመብልም መልካም” ነበር (ዘፍ 2፥9)። ሕይወት አካላዊ (ውጪአዊ) ብቻ ስላይደለ ከመኖርና ከመደሰት ያለፈ ደርዝ አለው፤ ነፍሳዊ፣ መንፈሳዊ ገጽታ። ይህም ደግሞ የተሟላ እንዲሆን በሚታየውና በሚበላው መካከል ምጡቅና ረቂቅ የሆነው አምላክ እንዲታሰብ፣ እንዲከበርም ታሰበ።
Add comment