[the_ad_group id=”107″]

“የውጭ ወራሪና የውስጥ ቦርቧሪ ያልናቸውን ትምህርቶች መግረዝ ይችላሉ ባይ ነኝ”

ተስፋዬ ሮበሌ ለትምህርት ከኢትዮጵያ እስኪወጣ ድረስ የተስፋ ዐቃቢያነ ክርስትና ማኅበርን በዳይሬክተርነት አገልግሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በዕቅበተ እምነት ርእሰ ጒዳዮች ላይ የተለያዩ መጻሕፍትንም ጽፏል፡፡ ከእነዚህም መካከል “የይሖዋ ምስክሮችና አስተምህሮአቸው በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘን”፣ “ውሃና ስሙ፡- ʻየሐዋርያት ቤተ ክርስቲያንʼ የድነት ትምህርት በቃለ እግዚአብሔር ሲመዘን”፣ “ዐበይት መናፍቃን” እንዲሁም “የዳቬንቺ ኮድ፡- ድርሳነ ጠቢብ ወይስ ድርሳነ ባልቴት?” ይጠቀሳሉ፡፡ ተካልኝ ዱጉማ በዕቅበተ እምነት ጕዳዮች ዙሪያ ከተስፋዬ ሮበሌ ጋር ያደረገው ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

Read More »

መንፈስ ቅዱስ በታሪክ ውስጥ

በዘመናችን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ምስባኮች ላይ መንፈስ ቅዱስ የሚለው ስም መጥራት የተለመደ ቢሆንም፣ ሕዝበ ክርስትያኑ ስለ መንፈስ ቅዱስ ማንነት ጠንቅቆ ያውቃል ለማለት አስቸጋሪ ይመስላል። መንፈስ ቅዱስን አስመልክቶ ግልጽ አስተምህሮ ያለም አይመስልም። ለአንዳንዶች መንፈስ ቅዱስ ተአምራት ማድረጊያ ኀይል፣ እንዲሁም በጨርቅ ተደርጎ እና በጠርሙስ ታሽጎ የሚወሰድ ትንግርት መፍጠሪያ ሲሆን፣ ለሌሎች ደግሞ ማነቃቂያ እና ተሃድሶ የሚያመጣ እሳት ወዘተ. ነው።

Read More »

እውን ክርስቲያኖች ሳይሞቱ ለዘላለም ሊኖሩ ይችላሉ?

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቴሌቪዥን መስኮት ብቻ እናውቃቸው የነበሩ አንዳንድ አፍሪካውያን “አገልጋዮች” በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መድረክ ላይ መታየት ጀምረዋል። በቅርቡ የተከሰቱ ሁለት ኩነቶችን እንኳ ብንመለከት “ሜጀር ሼፐርድ ፕሮፌት” ቡሽር ከማላዊ፣ “ነቢይ” ኮቦስ ቫን ሬንስበርግ ከደቡብ አፍርካ ወደ ኢትዮጵያ ያደረጉትን ጉብኝት ልብ ይሏል።

Read More »

“ዘመነ ነቢያት” በእግዚአብሔር ቃል ሲፈተሽ

ባለፈው ዕትም የ“ነቢይ” ቡሽሪን የኢትዮጵያ አገልግሎት አስመልክቶ አንድ መጣጥፍ አቅርቤ ነበር፡፡ የእኚህ ሰው “አገልግሎት” በሐሰት የተሞላና ከመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ጋር የሚጣረስ መሆኑን አሳይቻለሁ፡፡ እንዲህ ዐይነቱ የስህተት አስተምህሮ እንደ ቡሽሪ ባሉ ከውጭ ሀገር በሚመጡ አገልጋዮች ላይ ብቻ የሚታይ ሳይሆን በእኛ በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት እየተስተዋለ የመጣ ችግር ነው፡፡ የዛሬው መጣጥፍ የትኩረት አቅጣጫም ይህ ይሆናል፡፡

Read More »

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን የተጋፈጠቻቸው የኑፋቄ አስተምህሮዎች

የክርስትና እምነት ገና ከጅማሬው እውነተኛውን የክርስትናን አስተምህሮ በሐሰት ለመበረዝ በሚጥሩ የኑፋቄ ትምህርት መምህራን ከፍተኛ ተግዳሮት ይደርስበት እንደ ነበር ከመጽሐፍ ቅዱስን እንረዳለን፡፡ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ከሚገኙ መጻሕፍት መካከል አንድ ሦስተኛውን ስፍራ የሚወስደው ለመናፍቃን ትምህርት የተሰጠ ምላሽ እንደ ሆነ በዘርፉ ምርምር ያደረጉ የሥነ መለኮት ምሁራን ይጠቁማሉ፡፡

Read More »

ከሐሰተኛ ነቢያት ተጠበቁ!

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን በመሠረታዊ አቋሞቿ ላይ የአመለካከት ለውጥ እያመጣች እንደ ሆነ ይስተዋላል፡፡ ለውጡም ከእምነት ወደ ስሜታዊነት፣ ከተጨባጭ እውነት ወደ ሕልመኝነት እንዲሁም ከምክንያታዊነት ወደ ምሥጢር ናፋቂነት ዞራለች፡፡ ግን ለምን? ለምን በመጣው የትምህርት ንፋስ ሁሉ እንወሰዳለን? ለእነዚህ ጥያቄዎች መልሱ ዘርፈ ብዙ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ከእነዚህም ጥቂቶቹን ለማንሣት ያህል፡- እግዚአብሔርን ወደ መምሰል የሚያመራውን ንጹሕ የእግዚአብሔር ቃል ከማስተማር ይልቅ የራሳችንን ገድል በየምስባኩ ማውራታችን፣ ሕዝባችንን የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ሳይሆን የግለ ሰቦች ተከታይ ማድረጋችን እንዲሁም አማኙ ማኀበረ ሰብ ከምንም ነገር በላይ የተኣምራት ናፋቂዎች እንዲሆን ማድረጋችንና የመሳሰሉት ናቸው፡፡

Read More »
SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.