[the_ad_group id=”107″]

ቃለ መጠይቅ

” ‘መንፈስ ቅዱስ ካልተናገረ እኔ የምነግራችሁ አንዳች የለም’ ብሎ ጉባኤውን ማሰናበት ጤናማነት ነው”

መጋቢ መስፍን ሙሉጌታ በኮልፌ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን በመጋቢነት ያገለግላሉ። ከዚህ በተጨማሪ፣ ዘወትር ዓርብ ቤተ ክርስቲያኒቱ በምታዘጋጀው “የፈውስና ነጻ የማውጣት” መርሓ ግብር ላይ ላለፉት በርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል። በዚህ ዘመን በፈውስ ስጦታ ቤተ ክርስቲያንን ያገልግላሉ ከሚባሉት አገልጋዮች መካከል የመጋቢ መስፍን ስም ቀድሞ ይነሣል። ሕንጸት ስለ መንፈስ ቅዱስ፣ ስለ ስጦታዎቹ እና አጠቃቀሙ እንዲሁም ከዚሁ ጋር ተያይዘው ስለሚነሡ ጉዳዮች ከመጋቢ መስፍን ሙሉጌታ ጋር ያደረገው ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል።

Read More »

“ቤተ ክርስቲያን ለአእምሮ ሕሙማን ምቹ ቦታ ናት ብሎ ለመናገር አያስደፍርም”

እውቁ የሥነ አእምሮ ሐኪምና ተመራማሪ የሆኑት ፕሮፌሰር አታላይ ዓለም አሳሳቢነቱ ጨምሯል ስለሚባለው የአእምሮ ሕመም ከሕንጸት መጽሔት ጋር ቆይታ አድርገዋል። በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን አባል የሆኑት ፕሮፌሰር አታላይ፣ ችግሩን በተመለከተ በወንጌላውያን አማኞች መካከል ስላለው የአመለካከት ክፍተትና ሊደረጉ ስለሚገባቸው ርምጃዎች ሚክያስ በላይ እንደሚከተለው አነጋግሯቸዋል።

Read More »

“የውጭ ወራሪና የውስጥ ቦርቧሪ ያልናቸውን ትምህርቶች መግረዝ ይችላሉ ባይ ነኝ”

ተስፋዬ ሮበሌ ለትምህርት ከኢትዮጵያ እስኪወጣ ድረስ የተስፋ ዐቃቢያነ ክርስትና ማኅበርን በዳይሬክተርነት አገልግሏል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በዕቅበተ እምነት ርእሰ ጒዳዮች ላይ የተለያዩ መጻሕፍትንም ጽፏል፡፡ ከእነዚህም መካከል “የይሖዋ ምስክሮችና አስተምህሮአቸው በእግዚአብሔር ቃል ሲመዘን”፣ “ውሃና ስሙ፡- ʻየሐዋርያት ቤተ ክርስቲያንʼ የድነት ትምህርት በቃለ እግዚአብሔር ሲመዘን”፣ “ዐበይት መናፍቃን” እንዲሁም “የዳቬንቺ ኮድ፡- ድርሳነ ጠቢብ ወይስ ድርሳነ ባልቴት?” ይጠቀሳሉ፡፡ ተካልኝ ዱጉማ በዕቅበተ እምነት ጕዳዮች ዙሪያ ከተስፋዬ ሮበሌ ጋር ያደረገው ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

Read More »

“የሁላችን ድርሻ ተጠራቅሞ ነው ውጤት ያመጣነው”

ዘላላም አበበ በኢትዮጵያ ወንጌላውያን ክርስትያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማኅበር (ኢቫሱ) ውስጥ ለረጅም ዓመታት አገልግሏል፡፡ ለአራት ዓመታት በደቡብ አካባቢ የኢቫሱ ቢሮ በሙሉ ጊዜ አገልጋይነትና የአካባቢው ቢሮ አስተባባሪ በመሆንና ከ1996 ዓ.ም. እስከ 2007 ዓ.ም. ለዘጠኝ ዓመታት ደግሞ የማኅበሩ ዋና ጸሐፊ በመሆን አገልግሎ በቅርቡ በራሱ ፈቃድ የዋና ጸሐፊነት ሥራውን አስረክቧል። ወንድም ዘላለም በትምህርት ዝግጅቱ ከአዋሳ ዩኒቨርሲቲ፣ እርሻ ኮሌጅ በእርሻ ሥራ እንዲሁም ከኢቫንጄሊካል ቲዮሎጅካል ኮሌጅ የመጀመሪያ ዲግሪውን በነገረ መለኮት ያግኝቷል። ዘላለም በአሁኑ ሰዓት አሜርካን አገር በሚገኘው Gorden Conwell Theological Seminary በሥነ አመራር የድኅረ ምረቃ ትምህርት በመመላለስ እየተከታተለ ይገኛል፡፡ በኢቫሱ ውስጥ በነበረው አገልግሎቱና በተያያዙ ጉዳዮች አስናቀ እንድርያስ ከዘላለም አበበ ጋር ያደረገው ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

Read More »

ቃለ መጠይቅ ከአገኘሁ ይደግ ጋር

አገኘሁ ይደግ በኢትዮጵያ የወንጌላውያን አማኞች የዝማሬ አገልግሎት ውስጥ ስማቸው በቀዳሚነት ከሚነሡ ዘማሪያን መካከል የሚጠቀስ ነው። ዘመን ዘለቅ በሆኑት ዝማሬዎቹም ብዙዎች ተጽናንተዋል፣ ታንጸዋልም። የሕይወትን አስቸጋሪ ፈተናዎች በመቋቋም እግዚአብሔርን በጽናት ማገልገሉ ለአርኣያነት የሚያበቃው እንደ ሆነ የሚያውቁት ይናገራሉ። የዚህን ዘማሪ 25ኛ የአገልግሎትና 20ኛ የትዳር ዘመን በዓል ምክንያት በማድረግ ሕንጸት የቆይታ ዐምድ እንግዳ አድርጎታል። ጳውሎስ ፈቃዱ ከዘማሪ አገኘሁ ይደግ ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው ቀርቧል።

Read More »

“የክርስቲያን ሚዲያዎች ሲታዩና ተግባራቸው ሲገመገምም አብዛኛዎቹ አንባቢውንም ሆነ ተመልካቹን የማይመጥኑ…ሆነው እናገኛቸዋለን” – ቃለ መጠይቅ ከዶ/ር ንጉሤ ተፈራ ጋር

ሚክያስ በላይ ከዶ/ር ንጉሤ ተፈራ ጋር ባደረገው ቆይታ፣ አማኝ ማኅበረ ሰቡን በሚመለከት ስለ ኮሙኒኬሽንና የመገናኛ ብዙኅን አጠቃቀም፣ አብያተ ክርስቲያናት ከኅብረተ ሰቡ ጋር ስላላቸው መስተጋብር እንዲሁም በአጠቃላይ ከቤተ ክርስቲያንን አመራር ጋር ሊያያዙ በሚችሉ ጭብጦች ዙሪያ ያደረገው ቃለ ምልልስ እንደሚከተለው ቀርቧል።

Read More »

እኛ ከእግዚአብሔር ጋር የንግድ ስምምነት የለንም

መጋቢ ጻድቁ አብዶ፣ በኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ግንባር ቀደም ከሚባሉት አገልጋዮች መካከል የሚጠቀሱና ቤተ ክርስቲያኒቱን ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ ናቸው፡፡ ለስምንት ዓመታትም የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል አማኞች ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሐፊ ሆነው አገልግለዋል፡፡ በትምህርት ዝግጅታቸውም፣ ከኢስት አፍሪካ ስኩል ኦፍ ቲዮሎጂ (East Africa School of Theology) በነገረ መለኮት ጥናት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ያገኙ ሲሆን፣ በድኅረ ምረቃ መርሓ ግብር በሥልታዊ ነገረ መለኮት ጥናት (MTh in Systmatic Theology) በኢትዮጵያ የሥነ መለኮት ድኅረ ምረቃ ት/ቤት (EGST) ትምህርታቸውን ተከታትለዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል ሥነ መለኮት ሴሚናሪየም ፕሪንሲፓል ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡ ሚክያስ በላይ ከጴንጤቆስጤ አስተምህሮና ልምምድ ጋር በተያያዘ ከሚነሡ የስሕተት ትምህርቶች አኳያ እንዲሁም በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ለብዙዎች መነጋገሪያ ስለሆኑት “ሜጀር ሼፐርድ ፕሮፌት” ቡሽሪ አነጋግሯቸዋል፡፡

Read More »

“ጥበቡን ከእግዚአብሔር እና ከመንፈሳዊነቱ ውጪ ልተርከው አልችልም።”

“ጥበቡ፡- የምድረ በዳው እረኛ” በሚል ለንባብ የበቃው መጽሐፍ በብዙ ቅጂዎች ተባዝቶ መነበብ ከጀመረ አንድ ዓመት ሊሞላው ጥቂት ቀናት ቀርተውታል። ባለፉት ዐሥራ አንድ ወራትም በአገር ውስጥና ከአገር ውጪ በመጽሐፉ ይዘትና ቅርጽ ላይ የተለያዩ ውይይቶች ተካሄደዋል። በዋናነት በአንድ ቤተ ሰብ ሕይወት ላይ የሚያጠነጥነው ይህ መጽሐፍ የብዙዎችን ስሜት መግዛት እንደቻለም ይነገራል። ሰላማዊት አድማሱ ከጸሐፊዋ ወ/ሮ ሊሻን አጎናፍር ያደረገችው ቆይታ እንደሚከተለው ቀርቧል።

Read More »
SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.