
ስለ ብሽሽቅና ፉክክር ተኮር ስብከቶች
“ኢየሱስም ሆነ ሐዋርያትና ነቢያት፣ ግብዞችን በገሠጹበት ልክ መገሠጽ የምንችልበት ከሞራል ልዕልና የሚመነጭ ‘ሥልጣን’ ይኖረን እንደ ሆነ ራሳችንን መጠየቅ ያለብን ይመስለኛል።” ጌታሁን ሄራሞ
[the_ad_group id=”107″]
“ኢየሱስም ሆነ ሐዋርያትና ነቢያት፣ ግብዞችን በገሠጹበት ልክ መገሠጽ የምንችልበት ከሞራል ልዕልና የሚመነጭ ‘ሥልጣን’ ይኖረን እንደ ሆነ ራሳችንን መጠየቅ ያለብን ይመስለኛል።” ጌታሁን ሄራሞ
“በኢየሱስ የሆንን እኛ በሕይወት ነን፤ ማንም እርሱን በሕይወትነቱ ቢያውቀው በሕይወት ይኖራል። ሊያውቀው ባይወድድ ግን በሞት ይቀራል፤ መጨረሻውም ለዘላለም ከእግዚአብሔር የመለየት ቅጣት ይሆናል።” ዘሪቱ ከበደ
ለኦርቶዶክሳውያን አባቶች የተጻፈ ደብዳቤ፦ “ተንኳሽ ድምፅ ከመንግሥት ጋር በተጠጋጉ ሰዎቾቻችን ሲነገር ስሜታችሁን እጅጉን እንደሚነካው ከሰሞኑ ተምሬአለሁ። ይህን ለመረዳትም የምቸገር አይመስለኝም፤ ምክንያቱም እናንተ ከመንግሥት ጋር ተቀራርባችኋል ባልንበት ጊዜ አበጅታችኋል የሚል ስሜት አልተሰማንም ነበርና።” ባንቱ ገብረ ማርያም
“በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በወንጌላውያን አማኞች መካከል ያለውን ታሪካዊ የአግላይነት ውጥረት ይበልጡን የሚያከርሩ፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሚዛንና ብስለት ያጡ አስተምህሮቶች እንዲሁም ኢትዮጵያዊ ጨዋነት የጐደላቸው ሥነ ምግባራዊ ቀውሶች መታየት ከጀመሩ ሰንብተዋል። በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ፣ በእነዚሁ ሁለት ታላላቅ ቤተ እምነቶች ውስጥ ያለው የእርስ በእርስ መከፋፈል፣ ጐሣዊና ፖለቲካዊ ጽንፈኝነትን የተላበሰ በመሆኑ፣ የአገሪቱን ፈርጀ ብዙ መከራ የበለጠ አክብዶታል።” ግርማ በቀለ (ዶ/ር)
ሰሞኑን በማኅበራዊ ሚድያ ላይ መንፈሳዊ ስጦታዎችን በሚመለከት ብርቱ ሙግትና ውይይት እየተካሄደ አለ። ዛዲግ ብርሃኑ፣ ሰሞነኛ በሆነው ርእሰ ጕዳይ ላይ የሚከተለውን ዐሳብ አቅርቧል።
አማረ ታቦር፣ በዚህ ጽሑፉ የተለያዩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎችን በመጥቀስና የተለያዩ ታሪኮችን በማውሳት፣ በሰዎች ሕይወት ውስጥ የተገለጠውን የእግዚአብሔር የምሕረት ጥልቀትና ስፋት ያሳየናል። ተጨማሪ ያንብቡ፦
የክርስቶስ ስቃይ ያለ ጥርጥር ልዕለ ተፍጥሯዊ ፍትሕ ነው። ያሉትን የርኅራኄ ርዳታ ሁሉ ፍጹም የከለከል ፍትሕ ነው፤ የእግዚአብሔር አብ ፍቅር እንኳ እንዳይራራለት ያደረገ ፍትሕ ነው።
ዘሪቱ ከበደ በሦስት ተከታታትይ ክፍል በምታቀርበው ጽሑፍ፣ “ስለ እግዚአብሔር ሕዝብ” ምንነት እና መገለጫ ባሕርዩ ታስነብባለች፦ “ይህ ልዩ ሕዝብ በምድራዊ ልዩነቶቹ እንደገና ሊያዝና ሊከፋፈል የሚገባው ሕዝብም አይደለም። በክርስቶስ ከዓለም በተለየው ሕዝብ መካከል እንደ እግዚአብሔር ጥበብና መልካም ፈቃድ የሆነ ‘ልየታ’ እንጂ ልዩነት የለም።” ተጨማሪ ያንብቡ።
“አሁን ላይ፣ መከራው በኦርቶዶክስ እንደበዛባት፣ አንዳንዱንም መከራ በጋራ የተቀበልነው መሆኑን ሳስተውል፤ እንዲሁም እነርሱ (ኦርቶዶክሶቹ) እኛን የሚያሳድዱበት አጋጣሚ መኖሩን ስመለከት ለመደጋገፍ ዐብሮ መደራጀቱ ሊገፋበት እንደሚገባ ታይቶኛል።” የሚሉት ባንቱ ገብረ ማርያም፣ የግል ጕዟቸውን ባስቃኙበት በዚህ ጽሑፋቸው፣ ወንጌላውያንና ኦርቶዶክሳውያን ለመደጋገፍ አንድ ላይ የመደራጀታቸውን አስፈላጊነት ከተሞክሯቸው በመጥቀስ ይመክራሉ።
ዶ/ር ግርማ በቀለ በዚህ ጽሑፋቸው፣ ወንጌላውያን በጊዜ ሂደት እየተለማመዷቸው የመጡት ባሕላዊ እምነቶች ከወንጌል እምነት በተቃርኖ ያሉ ናቸው ሲል ይሞግታሉ። “የክርስቶስ ብቸኛ ቤዛዊ ሥራ ዋጅቶናል ስንል፣ ከኀጢአትና ባዕድ አምልኮ ጋር ትሥሥር ካለው ከየትኛውም ባሕል ጭምር ማለታችን ነው። . . . ይኸው እውነት በኢሬቻ ብቻ ላይ ሳይሆን፣ በሲዳማው ፍቼ ጨምበላላ፣ በወላይታው ጊፋታ፣ በሀዲያው ያሆዴ እንዲሁም በሌሎች ባሕላዊ በዓላት ላይ ባሉት ዕይታዎች ላይም አግባብነት አለው።” ይላሉ።
“በአግባቡ የተገራ ፈረስ ለባለቤቱ ክብር ያመጣል። ወደ ጦር ሜዳ ቢያደርስም፣ ዋንጫ ቢያሸንፍም፣ ታርሶበት ቢያመርትም፣ ግልቢያ ቢያሳምርም ትርፉና ክብሩ ለባለቤቱ ነው! . . . ሰው እንደ ፈረስ ነው። ያለ አለንጋና ያለ ልጓም አይኖርም። ልከኛው ባለአለንጋ ግን እግዚአብሔር ነው። ሲሻውም ልጓም ይሆናል።” ጳውሎስ ፈቃዱ።
ግርማ በቀለ (ዶ/ር)፣ የታዋቂውን እንግሊዛዊ የወንጌል ሰባኪና አስተማሪ ቻርልስ ሀደን ስፐርጀንን ግለ ታሪክ መነሻ አድርገው ባቀረቡት በዚህ ጽሑፍ፣ ስፐርጅን ያለፈበትን አስቸጋሪ የሕይወት ትግል፣ ስለ ወንጌል ንጽሕና ሲል የተጋፈጣቸውን ዕቡያን እንዲሁም፣ በጽናት የተደመደመውን የድል ሕይወት ያስቃኙናል።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.