
ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ሲሰጥ የቈየው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥልጠና ተጠናቀቀ
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
[the_ad_group id=”107″]
የሕንጸት መጽሐፍ ክበብ ላለፉት ዐሥርት ዓመታት ሲያከናውናቸው የነበረውን ተግባር ለመዘከር የ10ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሰኔ 4 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. ልዩ በሆነ መርሓ ግብር አከበረ። ክብረ በዓሉ በኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድኅረ ምረቃ ት/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ የተከናወነ ሲሆን፣ ጥሪ የተደረገላቸው የመጽሐፍ ክበቡ አባላት እና የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር ቤተ ሰቦች ተገኝተዋል።
ሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ፣ ሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች መካከል “የውይይትና ሥልጠና መድረኮችን ማዘጋጀት በተሰኘው የአገልግሎት ክፍል ሥር የሚካተት ሲሆን፣ የንባብ ባሕል እንዲዳብር የበኵሉን አስተዋጽኦ በማድረግ ላይ ይገኛል።
በክብረ በዓሉ እንደተወሳውም ሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ “ቤሪያ” በተሰኘ ስያሜ በ2004 ዓ.ም. ወርኀዊ በሆነ መርሓ ግብር መጻሕፍትን በመገምገም የዐሳቡ ጠንሳሽ በሆነው ዳዊት ጸጋዬ የተጀመረ ነበር። በ2005 ዓ.ም. ተቋማዊ በሆነ መልኩ በሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር ሥር የሚካሄድ ቋሚ መርሓ ግብር በመሆን መቀጠል ችሏል።
በክብረ በዓሉ የመጽሐፍ ክበቡ የዐሥር ዓመታት ቈይታ በፎቶ ኤግዚቢሽን እና በጽሑፎች የተወሳ ሲሆን፣ የመጽሐፍ ክበቡ ታዳሚያን ስለ መጽሐፍ ክበቡ ምልከታቸውን እና የወደ ፊት ምኞታቸውን አጋርተዋል። በመርሓ ግብሩ ማጠቃለያ፣ ባለፉት ዐሥርት ዓመታት ለመጽሐፍ ክበቡ ልዩ ልዩ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ተቋማት እና ግለ ሰቦች የምስክር ወረቀት የተበረከተ ሲሆን፣ ለመጽሐፍ ክበቡ መመሥረት ጕልሕ ሚና ለነበረው ዳዊት ጸጋዬ እጅግ ላቅ ያለ ዕውቅና ተሰጥቷል።
ይህ መርሓ ግብር፣ ሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር ከተመሠረተ 10ኛ ዓመቱን መያዙን አስመልክቶ ከሚያከናውናቸው ዝግጅቶች መካከል የመጀመሪያው ነው።
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
የሕንጸት መጽሐፍ ክበብ ላለፉት ዐሥርት ዓመታት ሲያከናውናቸው የነበረውን ተግባር ለመዘከር የ10ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሰኔ 4 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. ልዩ በሆነ መርሓ ግብር አከበረ። ክብረ
“የቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት” የተሰኘ የግማሽ ቀን ሥልጠና ለተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች ተሰጠ። በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ሥልጠና፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 14 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በላቭ ኤንድ ኬር ማዕከል የተካሄደ ነበር።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
1 comment
የአስር አመት ጉዞን ማሰብ እና ለዚህ ለመብቃት ምክንያት የሆነውን ጌታ ማመስገን ደስ ይላል::ሕንጸት ከትናንት በበለጠ ብዙ ተጋድሎ የሚጠይቁ አመታት ከፊቷ እንዳሉ እረዳለሁ ለዚህ ደግሞ መፍትሔው አብረን በመቆም መጽናት ነው::