[the_ad_group id=”107″]

“አምልኮና ሀልዎተ እግዚአብሔር” የተሰኘው መጽሐፍ ውይይት ተካሄደበት

April 11, 2016
“አምልኮና ሀልዎተ እግዚአብሔር” የተሰኘው መጽሐፍ ውይይት ተካሄደበት

“አምልኮና ሀልዎተ እግዚአብሔር” በሚል በእንዳልካቸው ሐዋዝ የተጻፈው መጽሐፍ እሑድ ሚያዚያ 2 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. በ9 ሰዓት በኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድኅረ ምረቃ ትምህርት ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ ውይይት ተካሄደበት፡፡

ለውይይት መነሻ ጽሑፍ ያቀረበው አቶ አዳነ አስናቀ ሲሆን፣ መጽሐፉ ከይዘትም ሆነ ከቅርጽ አንጻር ሊሻሻል ይገባል ያላቸውን ክፍተቶች፣ ብርቱ ናቸው ካላቸው ሐሳቦች ጋር አያይዞ አቅርቧል፡፡ ይህንን ተከትሎም ታዳሚያን ለጸሐፊው በርካታ ጥያቄዎችንና አስተያቶችን አቀርበዋል፡፡

የመጽሐፉ ጸሐፊ እንዳልካቸው ሐዋዝ ከገምጋሚውና ከታዳሚያን ለተነሡለት ጥያቄዎች መልስ ይሆናል ያለውን የሰጠ ሲሆን፣ ከግምገማውም ሆነ ከታዳሚያን ከቀረቡለት አስተያየቶች ጠቃሚ ትምህርት ማግኘቱንና ወደፊት መጽሐፉ ለዳግም ኅትመት ሲቀርብ የሚያስተካክላቸው ነገሮች እንዳሉት ጭምር ተናግሯል፡፡

በመጪው ግንቦት 7 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. ለውይይት የሚቀርበው መጽሐፍ በመጋቢ ስሜ ታደሰ የተጻፈውና “ምን ሠርተን እንለፍ?” የተሰኘው መጽሐፍ መሆኑ በዕለቱ ተገልጿል፡፡

Add comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Latest News

ስለ ቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ሥልጠና ተሰጠ

“የቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት” የተሰኘ የግማሽ ቀን ሥልጠና ለተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች ተሰጠ። በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ሥልጠና፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 14 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በላቭ ኤንድ ኬር ማዕከል የተካሄደ ነበር። 

Read More »
SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.