
ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ሲሰጥ የቈየው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥልጠና ተጠናቀቀ
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
[the_ad_group id=”107″]
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
ሥልጠናው የተሰጠው ከተለያዩ ቤተ እምነት ለመጡ የሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ሲሆን፣ ሠልጣኞቹ በአገልግሎት ስፍራቸው ሳሉ አገልግሎታቸውን በተሻለ መልኩ ማካሄድ እንዲችሉ የሚያስችሏቸውን መጽሐፍ ቅዱሳዊና ሥነ መለኮታዊ ኮርሶች እንዲያገኙ የሚያስችሏቸው ናቸው ተብሏል። ሥልጠናው ላለፉት ሦስት ዓመታት በአዳማ ከተማ ሲሰጥ የቈየ ሲሆን፣ ተማሪዎቹ ወደ አካባቢያቸው በመሄድ በዐሥራ ስድስት ቡድኖች ውስጥ ያሉ 256 ተማርዎችን በማሠልጠን ላይ መሆናቸው ተገልጿል።
“BEE World” መቀመጫውን በአሜሪካን አገር ያደረገ ለትርፍ ያልተቋቋመ ተቋም ሲሆን፣ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች ላሉና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥልጠና ላላገኙ አገልጋዮች በፓስቶራል ሚኒስትሪ ዲፕሎማ፣ በቲዮሎጂና ቸርች ሊደርሺፕ አሶሺዬት ዲግሪ እንዲሁም በቲዮሎጂ የመጀመሪያ ዲግሪ የሚሰጥ አገልግሎት ነው።
የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያ በዳላስ ከBEE World ጋር በአጋርነት ሲሰጡ የቆዩት ሥልጠና፣ በቀጣይነት በደብረ ብርሃን ከተማ የሚሰጥ ሲሆን፣ ከአካባቢው የሚመጡ የሙሉ ጊዜ አገልጋዮች በሠልጠናው ተካፋይ እንደሚሆኑ ለሕንጸት የተደረሰው መረጃ ያስረዳል።
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
የሕንጸት መጽሐፍ ክበብ ላለፉት ዐሥርት ዓመታት ሲያከናውናቸው የነበረውን ተግባር ለመዘከር የ10ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሰኔ 4 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. ልዩ በሆነ መርሓ ግብር አከበረ። ክብረ
“የቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት” የተሰኘ የግማሽ ቀን ሥልጠና ለተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች ተሰጠ። በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ሥልጠና፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 14 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በላቭ ኤንድ ኬር ማዕከል የተካሄደ ነበር።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment