
ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ሲሰጥ የቈየው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥልጠና ተጠናቀቀ
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
[the_ad_group id=”107″]
በመጽሐፍ ቅዱስ ሠራዊት ዓለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን – ዛየን ቻፕል አዘጋጅነት “የክርስቲያን ፌስቲቫል ኢትዮጵያ 2008” የተሰኘ ዝግጅት ከታኅሣሥ 15 እስከ 17 2008 ዓ.ም. ድረስ በአዲስ አበባ መካነ ኢየሱስ ሴሚናሪየም ቅጥር ግቢ ውስጥ እንደሚካሄድ ተገለጸ፡፡ ፌስቲቫሉን ሠላሳ ሺህ የሚደርሱ ሰዎች ይጎበኙታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡
ታኅሣሥ 1 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. በሳሮ ማሪያ ሆቴል በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደ ተገለጸው፣ የዝግጅቱ ቀዳሚ ዐላማ “ወንጌልን ለትውልድ ለማድረስ የዳበረ፣ ሁለንተናዊ አቅም ያለው እና የተጣመረ ማኅበረ ሰብ መፍጠር” መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን፣ ከዚህ በተጨማሪም የክርስቲያን ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት ትሥሥርን ማጎልበት ትልቅ ትኩረት የሚሰጠው ተግባር መሆኑን የፌስቲቫሉ አዘጋጅ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ ማቲያስ ሠረቀ ብርሃን ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
ፌስቲቫሉ ስለሚኖሩት መርሓ ግብሮች ዝርዝር ማብራሪያ የሰጡት የአዘጋጅ ቡድን አባል የሆኑት አቶ ዮሴፍ ጥላሁን ናቸው፡፡ አብያተ ክርስቲያናት፣ የተለያዩ ግብረ ሠናይ ድርጅቶችና የንግድ ተቋማት ራእያቸውን፣ አገልግሎታቸውንና ምርታቸውን የሚያስተዋውቁበት ዐውደ ርእይ፣ የክርስቲያን ነጋዴዎች የእርስ በእርስ የንግድ ውይይት፣ ለሕፃናት እና ወጣቶች የሚሆኑ አዝናኝና አስተማሪ ዝግጅቶች፣ ዝማሬዎችና የቃለ እግዚአብሔር ስብከቶች እንደሚኖሩ አቶ ዮሴፍ በመግለጫው ላይ ተናግረዋል፡፡
የመጽሐፍ ቅዱስ ሠራዊት ዓለም አቀፍ ቤተ ክርስቲያን በ1988 ዓ.ም. በኢትዮጵያ የተቋቋመችና በአዲስ አበባ ሰባት የሚደርሱ አጥቢያዎች እንዲሁም ከአትዮጵያ ውጪ ሁለት እንዷላት የፌስቲቫሉ አዘጋጅ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ዋና መጋቢ የሆኑት መጋቢ ካሌብ ተድላ ገልጸዋል፡፡
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
የሕንጸት መጽሐፍ ክበብ ላለፉት ዐሥርት ዓመታት ሲያከናውናቸው የነበረውን ተግባር ለመዘከር የ10ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሰኔ 4 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. ልዩ በሆነ መርሓ ግብር አከበረ። ክብረ
“የቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት” የተሰኘ የግማሽ ቀን ሥልጠና ለተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች ተሰጠ። በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ሥልጠና፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 14 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በላቭ ኤንድ ኬር ማዕከል የተካሄደ ነበር።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment