[the_ad_group id=”107″]

ኢቫሱ አምስተኛውን “የክርስቶስ ልዕቀት ጉባኤ” አካሄደ

March 17, 2019
ኢቫሱ አምስተኛውን “የክርስቶስ ልዕቀት ጉባኤ” አካሄደ

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማኅበር (ኢቫሱ) አምስተኛውን የክርስቶስ ልዕቀት ጉባኤ ላለፉት ሦስት ቀናት በቤዛ ኢንተርናሽናል ቤተ ክርስቲያን መሰብሰቢያ አዳራሽ ሲያካሂድ ቆይቷል።

ከመጋቢት 6 – 8፥ 2011 ዓ.ም. በተካሄደው በዚሁ ዓመታዊ ጉባኤው ላይ እስከ ሁለት ሺህ የሚደርሱ ተማሪዎች እንደተገኙ ከማኅበሩ ጽ/ቤት ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል። ተማሪዎቹ በአዲስ አበባ፣ አምቦ፣ ወልቂጤ፣ ፍቼ፣ ደብረ ብርሃን፣ አዳማ፣ አሰላ እና ወሊሶ ውስጥ ካሉ የመንግሥትና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመጡ ናቸው ተብሏል።

የዘንድሮው ጉባኤ መሪ ጥቅስ “ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” (የሐዋርያት ሥራ 1፥8) ሲሆን፣ በሦስቱ ቀናት ለተማሪዎቹ ይቀርቡ የነበሩ መልእክቶችና ትምህርቶችም በዚሁ ጭብጥ የተቃኙ ነበሩ። ኢቫሱ በመላ አገሪቱ እስከ አምሳ ሺህ የሚደርሱ የወንጌል አማኝ ተማሪዎችን የሚያስተባብር ማኅበር ሲሆን፣ በአፍሪካ ውስጥ ካሉ የተማሪ አገልግሎቶች ውስጥ ትልቁ እንደ ሆነም ይነገርለታል።

Add comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Latest News

ስለ ቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ሥልጠና ተሰጠ

“የቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት” የተሰኘ የግማሽ ቀን ሥልጠና ለተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች ተሰጠ። በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ሥልጠና፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 14 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በላቭ ኤንድ ኬር ማዕከል የተካሄደ ነበር። 

Read More »
SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.