
ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ሲሰጥ የቈየው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥልጠና ተጠናቀቀ
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
[the_ad_group id=”107″]
“ፈለገ ብርሃኑ” የተሰኘው መጽሐፍ በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት በሚካሄደው ወርኀዊ የመጽሐፍ ግምገማ መርኀ ግብር ላይ ቀርቦ ውይይት ተደረገበት፡፡ እሑድ ኅዳር 5 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድኀረ ምረቃ ት/ቤት መሰብሰቢያ አደራሽ በተደረገው በዚህ የውይይት መድረክ ላይ የመጽሐፉ ጸሐፊ ተገግኝቶ ለቀረቡለት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ለውይይት መነሻ የሚሆን ሐሳብ አቀርበው የነበሩት መጋቢ በቀለ ወልደ ኪዳን ሲሆኑ፣ ስለ መጽሐፉ አቀራረብ፣ ስለ ጸሐፊው፣ ስለ ባለ ታሪኩ እንዲሁም በመጽሐፉ ቅርጽ ላይ ዳሰሳቸውን አቀርበዋል፡፡
“ፈለገ ብርሃኑ” ግለ ታሪክ የመጽሐፍ ዘውግ ሲሆን፣ የታሪኩ ባለቤት በሆኑትና በኢትዮጵያ ብርሃነ ወንጌል መጥምቃውያን ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም “ኤክሌሺያ ተነሽ” በተሰኘው የአገልግሎት ማኅበር በሚታወቁት በዶ/ር ብርሃኑ ሀብቴ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን መጽሐፍ ነው፡፡ መጽሐፉ ግለ ሰቡ ለክርስቶስ ወንጌል የነበራቸውን መሰጠትና ፍቅር የሚያሳይ ሲሆን፣ የልጅነት ታሪካቸውን፣ እንዴት ወደ ጌታ እንደ መጡና በቀደሙት ዘመናት ስለ ነበራቸው የአገልግሎት ዘመን፣ ስለ ቤተ ሰብ ሕይወታቸው፣ወዘተ. የሚያወጋ መጽሐፍ ነው፡፡
በዕለቱ በተደረገው ውይይት ላይ የባለ ታሪኩ የትዳር ጓደኛ እና ሁለት ልጆቻቸው የተገኙ ሲሆን፣ ከዚህ በተጨማሪ ግለ ሰቡን የሚያውቁና የቅርብ ወዳጅ ከነበሩ መካከል የተገኙ ሰው ስለ ባለ ታሪኩ ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡
በቀጣዩ ወር፣ ታኅሣሥ 3 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. ለውይይት የሚቀርበው መጽሐፍ በኀይል ከበደ የተጻፈውና “ፌሽታ እና ጉርሻ” የተሰኘው “ትርጉምና ወጥ ቁርጥራጭ ወጎች፣ መጣጥፎች፣ አጫጭር ልብወለድና እውነታኛ ታሪኮች”ን የያዘ መጽሐፍ መሆኑ በዕለቱ ተነግሯል፡፡
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
የሕንጸት መጽሐፍ ክበብ ላለፉት ዐሥርት ዓመታት ሲያከናውናቸው የነበረውን ተግባር ለመዘከር የ10ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሰኔ 4 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. ልዩ በሆነ መርሓ ግብር አከበረ። ክብረ
“የቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት” የተሰኘ የግማሽ ቀን ሥልጠና ለተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች ተሰጠ። በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ሥልጠና፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 14 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በላቭ ኤንድ ኬር ማዕከል የተካሄደ ነበር።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment