
ሕንጸት እና ሕይወት ቲቪ በጋራ ለመሥራት ተስማሙ
ሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር፣ ለዕይታ የሚያቀርባቸው የቪዲዮ ዝግጅቶቹ በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን አዘጋጅነት በሚቀርበውና፣ በቅርቡ መደበኛ ሥርጭቱን በጀመረው የሕይወት ቲቪ ላይ እንዲተላለፍ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከቤተ ክርስቲያኒቱ ጋር አደረገ።
[the_ad_group id=”107″]
የመሠረተ ክርስቶስ ቤተ፣ በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ የጥር ወር የመጽሐፍ ግምገማ መርሓ ግብር ላይ ቀርቦ በነበረውና፣ “የተከዳው እውነት” በተሰኘው መጽሐፍ ላይ ስሟ ያለ አግባብ መነሣቱን በመግለጽ፣ ዕርማት እንዲወሰድ ጠይቃለች። የቤተ ክርስቲያናቱ ደብዳቤ እንደሚከተለው ቀርቧል፦
ቀን 24/06/2015
ቁጥር መክቤክ 01/587/2015
ለሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ
አዲስ አበባ
የሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ በተለያዩ ግለ ሰቦች የተጻፉና ለሕዝብ ይጠቅማሉ የተባሉ መጽሐፎችን በመገምገም ጸሐፊዎችንና አንባቢዎች በጥሩ አመለካከት እንዲታነጹ በማድረግ የተቀደሰ ስራ የሚሰራ እንደሆነ ይታወቃል። ለዚህ እግዚአብሔር አብዝቶ ይባርካችሁ በርቱ ማለት እንፈልጋለን።
በዚሁ የመጽሐፍ ክበብ በጥር ወር ላይ፣ “የተከዳ እውነት” በሚል በቀረበውና በመጋቢ ስሜ ታደሰ የተጻፈ መጽሐፍ ግምገማ ላይ የተገኙት የመጽሐፉ ጸሐፊ “መሠረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ካልቪናዊ ቤተክርስቲያን ነች” በማለት በምንም ዓይነት ሁኔታ የማይወክላትን የራሳቸውን እይታ የቤተክርስቲያኗ እምነትና ልምምድ አድርገው ተናግረዋል።
የመሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን አንድም ቀን እኛ ካልቪን ነን ወይም አርሚን ነን ብላ አስተምራ አታውቅም። ከሁለቱም ጎራ ባትሆንም አመጣጧ ከአናባፕቲስት ስትሆን ሰዎች ለመዳን ክርስቶስ ኢየሱስን ማመን እንዳለባቸው/እንደሚጠበቅባቸው/፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞት ለሁሉም ሰው እንጂ ለተወሰኑ ምርጦች ብቻ እንዳልሆነ፣ ሰው የተሰጠውን በወንጌል የማመን ዕድል ሊጠቀም ወይም ላይጠቀም እንደሚችል፣ ሰው የተዘጋጀለትን የዘላለም ክብር ለማግኘት መጽናት እንደሚገባው የእግዚአብሔርም ጸጋ ለዚህ እንደሚረዳው ታምናለች ታስተምራለች።
ስለዚህ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ካልቪናዊት ነች የሚለው የተሳሳተ ፍረጃ በቀረበበት የሕንጸት መድረክ ላይ የተሳሳተ ገለጻ እንደሆነ ታውቆ ማስተካከያ እንዲደረግ እየጠየቅን የትምህርትና ስልጠና መምሪያ በቅርበት እንዲከታተል ግልባጭ ተደርጎለታል።
ከመንፈሳዊ ሰላምታ ጋር
ደሳለኝ አበበ ኢጆ (ፓስተር)
ፕሬዚዳንት
ሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር፣ ለዕይታ የሚያቀርባቸው የቪዲዮ ዝግጅቶቹ በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን አዘጋጅነት በሚቀርበውና፣ በቅርቡ መደበኛ ሥርጭቱን በጀመረው የሕይወት ቲቪ ላይ እንዲተላለፍ የሚያስችለውን የመግባቢያ ስምምነት ከቤተ ክርስቲያኒቱ ጋር አደረገ።
በኢትዮጵያ ያሉ የሃይማኖት ተቋማት በአገርና ሰላም ግንባታ ላይ ሊጫወቱ ስለሚችሉት ሚና የፓናል ውይይት፣ ቅዳሜ ጥር 13 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. ተካሄደ። ሙሉ ቀን በፈጀው በዚህ የፓናል
በሕንጸት የመጽሐፍ ዕውቅና ሥነ ሥርዐት ላይ ከተወሰዱ ፎቶዎች መካከል (ፎቶ በገናዬ ዕሸቱ)
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
2 comments
ተባረኩ
Necessary issue thank you Paul’s