
ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ሲሰጥ የቈየው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥልጠና ተጠናቀቀ
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
[the_ad_group id=”107″]
“365 ቀናት፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ በየዕለቱ” የተሰኘና በዐይነቱ ልዩ የሆነ የጥሞና መጽሐፍ ለንባብ ቀረበ። በነገረ መለኮት መምህሩ እንዳሻው ነጋሽ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ፣ እሑድ ነሐሴ 29 ቀን፥ 2014 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድኅረ ምረቃ ት/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል።
መጽሐፉ ለኅትመት የበቃው፣ ከመስከረም 1 ቀን፥ 2014 ዓ.ም. ጀምሮ፣ እስከ አሁን በዘለቀውና የፊታችን ቅዳሜ ጷጕሜ 5 ቀን፥ 2014 ዓ.ም. እንደሚጠናቀቅ በሚጠበቀው ዕለታዊ ጥሞና ላይ ይቀርቡ የነበሩና የሚቀርቡ ትምህርቶች በአንድ ላይ የተካተቱበት ነው።
ጸሐፊው እንዳሻው ነጋሽ በከፈተው የቴሌግራም ቻናል በኩል፣ ለዓመቱ ያወጣውን ዕለታዊ የንባብ መርሓ ግብር ተከትለው፣ ዐብረው ያነብቡ የነበሩ በሺሕዎች የሚቈጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት መሆኑ በምረቃ ሥነ ሥርዐት ላይ ተጠቅሷል። መጽሐፉ፣ በየዕለቱ የሚነበቡ ሦስት ምዕራፎችን፣ የምዕራፎቹን ዕጣሬ፣ ከንባብ የተገኙ ትምህርቶችንና የጸሎት ርእሶችን የያዘ ነው። ስድስት መቶ ሰማኒያ አራት ገጾች ያሉት ይህ መጽሐፍ፣ አማኞች መጽሐፍ ቅዱስን ወጥ በሆነ መልኩ እንዲያነብቡ ከማስቻሉም በላይ፣ ያነበቡትን እንዲያሰላስሉና በሕይወታቸው ተግባራዊ እንዲያደርጉት የሚያግዝ መሆኑ ተነግሮለታል። መጽሐፉ፣ በዐምስት መቶ ብር ለሽያጭ ቀርቧል።
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
የሕንጸት መጽሐፍ ክበብ ላለፉት ዐሥርት ዓመታት ሲያከናውናቸው የነበረውን ተግባር ለመዘከር የ10ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሰኔ 4 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. ልዩ በሆነ መርሓ ግብር አከበረ። ክብረ
“የቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት” የተሰኘ የግማሽ ቀን ሥልጠና ለተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች ተሰጠ። በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ሥልጠና፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 14 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በላቭ ኤንድ ኬር ማዕከል የተካሄደ ነበር።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment