
የ2015 ዓ.ም. ሕንጸት የመጽሐፍ ዕውቅና ሥነ ሥርዐት በፎቶ
በሕንጸት የመጽሐፍ ዕውቅና ሥነ ሥርዐት ላይ ከተወሰዱ ፎቶዎች መካከል (ፎቶ በገናዬ ዕሸቱ)
[the_ad_group id=”107″]
“365 ቀናት፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ በየዕለቱ” የተሰኘና በዐይነቱ ልዩ የሆነ የጥሞና መጽሐፍ ለንባብ ቀረበ። በነገረ መለኮት መምህሩ እንዳሻው ነጋሽ የተጻፈው ይህ መጽሐፍ፣ እሑድ ነሐሴ 29 ቀን፥ 2014 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድኅረ ምረቃ ት/ቤት መሰብሰቢያ አዳራሽ፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ተመርቋል።
መጽሐፉ ለኅትመት የበቃው፣ ከመስከረም 1 ቀን፥ 2014 ዓ.ም. ጀምሮ፣ እስከ አሁን በዘለቀውና የፊታችን ቅዳሜ ጷጕሜ 5 ቀን፥ 2014 ዓ.ም. እንደሚጠናቀቅ በሚጠበቀው ዕለታዊ ጥሞና ላይ ይቀርቡ የነበሩና የሚቀርቡ ትምህርቶች በአንድ ላይ የተካተቱበት ነው።
ጸሐፊው እንዳሻው ነጋሽ በከፈተው የቴሌግራም ቻናል በኩል፣ ለዓመቱ ያወጣውን ዕለታዊ የንባብ መርሓ ግብር ተከትለው፣ ዐብረው ያነብቡ የነበሩ በሺሕዎች የሚቈጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት መሆኑ በምረቃ ሥነ ሥርዐት ላይ ተጠቅሷል። መጽሐፉ፣ በየዕለቱ የሚነበቡ ሦስት ምዕራፎችን፣ የምዕራፎቹን ዕጣሬ፣ ከንባብ የተገኙ ትምህርቶችንና የጸሎት ርእሶችን የያዘ ነው። ስድስት መቶ ሰማኒያ አራት ገጾች ያሉት ይህ መጽሐፍ፣ አማኞች መጽሐፍ ቅዱስን ወጥ በሆነ መልኩ እንዲያነብቡ ከማስቻሉም በላይ፣ ያነበቡትን እንዲያሰላስሉና በሕይወታቸው ተግባራዊ እንዲያደርጉት የሚያግዝ መሆኑ ተነግሮለታል። መጽሐፉ፣ በዐምስት መቶ ብር ለሽያጭ ቀርቧል።
በሕንጸት የመጽሐፍ ዕውቅና ሥነ ሥርዐት ላይ ከተወሰዱ ፎቶዎች መካከል (ፎቶ በገናዬ ዕሸቱ)
የሥላሴያውያን መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር ያሳተመው “አዲስ ኪዳንና መጽሐፈ መዝሙር” የተሰኘ መጽሐፍ ቅዱስ ተመረቀ።
ከተመሠረተ ሃያ ዐምስት ዓመታትን ያስቈጠረው የኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድኅረ ምረቃ ት/ቤት፣ ዛሬ ኅዳር 23 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በትምህርት ቤቱ መሰብሰቢያ አድራሽ የኢዮቤልዩ በዓሉን መዝጊያ ሥነ ሥርዐት አካሄዷል።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment