
ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ሲሰጥ የቈየው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥልጠና ተጠናቀቀ
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
[the_ad_group id=”107″]
ሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ በመስከረም 2008 ዓ.ም. ወርኀዊ መርሓ ግብሩ የሚካኤል ሽፈራውን “ወፍ ማስፈራሪያ እና ሌሎች አጫጭር ታሪኮች” የተሰኘውን መጽሐፍ በኢትዮጵያ ሥነ መለኮት ድኅረ ምረቃ ት/ቤት መሰብሰቢያ አደራሽ ለውይይት አቀረበ፡፡
ለውይይት መነሻ የሚሆን ጽሑፍ ያቀረበው ሠርፀ ፍሬ ስብሃት ሲሆን፣ ደራሲ ሚካኤል ይዞት የቀረበው ሥራ በኢትዮጵያ የሥነ ጽሑፍ ዘውግ ውስጥ እጁግን ያልተለመደና ተገቢውን ስያሜ እንኳን ያለገኘ እንደ ሆነ ጠቁሟል፡፡ አያይዞም፣ መጽሐፉ ዕምቅ ፍልስፍናዊ እና ሃይማኖታዊ ሐሳቦችን የያዘ ከመሆኑ ባሻገር በእንስሳት/ዕፅዋት አፍ በሚነገር የትርክት ዘዬ እውነትን የሚያስሱ ታሪኮች የታከተቱባቸው ሥራዎች መሆናቸውን አመለክቷል፡፡
የመጽሐፉ ጸሐፊ ሚካኤል ሽፈራው ከታዳሚያን ለተነሡለት ጥያቄዎች በሰጠው ምላሽ፣ ታሪኮቹ በ1987 ዓ.ም. ላይ የተጻፉ እንደነበሩና ከራሱ የግል ሕይወት ጥያቄ ተነሥቶ እንደ ጻፈው ተናግሯል፡፡ “ታሪኮቹ ተስፋን አይሰጡም፤ ጨለምተኞች ናቸው” በሚል ለተነሣለት ጥያቄ ምላሽ ሲሰጥም፣ በወቅቱ መጽሐፉን በሚጽፍበት ጊዜ የነበረበት ስሜት ይህንኑ የሚመስል እንደ ነበረ ከጠቆመ በኋላ፣ “በመፍረስ እና እንደ ገና በመሠራት ሂደት ውስጥ” ያለ ሰው ጥያቄዎችን የሚወክሉ ታሪኮች ናቸው ሲል ምላሽ ሰጥቷል፡፡
ሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ በመጪው ጥቅምት 7 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. ለውይይት የሚያቀርበው መጽሐፍ በጸጋአብ በቀለ የተጻፈውና “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ተሐድሶ” የተሰኘው መሆኑ ተነግሯል፡፡
በመጨረሻም፣ አያት የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) አካባቢ በሚገኘው “አያት ጨፌ አንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ የሕዝብ ት/ቤት” ውስጥ ለሚማሩና ቤተ ሰቦቻቸው በችግር ላሉ ተማሪዎች የትምህርት መርጃ መሣሪያዎችን ለመስጠት መታሰቡንና የመጽሐፍ ክበቡ ታዳሚያን አቅማቸው የፈቀደውን ያህል እገዛ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል፡፡ በዚህም መሠረት የትምህርት መርጃ መሣሪያዎቹን በመጪው ጥቅምት 7 ቀን፣ 2008 ዓ.ም. በሚደረገው የመጽሐፍ ውይይት መርሓ ግብር ላይ ይዞ መምጣት እንደሚቻል አስተባባሪዎቹ ገልጸዋል፡፡
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
የሕንጸት መጽሐፍ ክበብ ላለፉት ዐሥርት ዓመታት ሲያከናውናቸው የነበረውን ተግባር ለመዘከር የ10ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሰኔ 4 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. ልዩ በሆነ መርሓ ግብር አከበረ። ክብረ
“የቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት” የተሰኘ የግማሽ ቀን ሥልጠና ለተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች ተሰጠ። በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ሥልጠና፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 14 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በላቭ ኤንድ ኬር ማዕከል የተካሄደ ነበር።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment