
ለሙሉ ጊዜ አገልጋዮች ሲሰጥ የቈየው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሥልጠና ተጠናቀቀ
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
[the_ad_group id=”107″]
የቀድሞ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማኅበር (ኢቫሱ) ዋና ጸሐፊ የነበረው አቶ ዘላለም አበበ፣ ለዓለም አቀፉ የወንጌላውያን ተማሪዎች ኅብረት (IFES-EPSA) የአፍሪካ ዋና ጸሐፊ ሆኖ ተሰየመ፡፡ ሹመቱን ተከትሎም የተቋሙ ጽሕፈት ቤት ከናይጄሪያ ወደ አዲስ አበባ እንደሚዘዋወር ለማወቅ ተችሏል፡፡
ኀላፊነቱን ከዛሬ ኖቬምበር 1 ቀን፣ 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ሙሉ በሙሉ የሚጀምረው አቶ ዘላለም፣ ከትላንት በስቲያ በታንዛኒያ ዳሬ ሰላም የርክክብ ሥነ ሥርዐት ፈጽሟል፡፡ ዘላለም ለዚህ ኀላፊነት ከመብቃቱ ቀደም ብሎ የተቋሙ ተባባሪ ጸሐፊ በመሆን የሚሲዮን እና ደቀ መዝሙር ሥራ ክፍልን ለጥቂት ጊዜ ያህል በማስተባበር ላይ ሲሠራ እንደ ቆየ በሹመት ደብዳቤው ላይ ተጠቅሷል፡፡
አቶ ዘላለም አበበ በተማሪዎች አገልግሎት ውስጥ ከዐሥራ ስድስት ዓመታት በላይ ሲሳተፍ ከመቆየቱም በላይ፣ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ተማሪዎችና ምሩቃን ማኅበር (ኢቫሱ) ዋና ጸሐፊ በመሆን ለዘጠኝ ዓመታት አገልግሏል፡፡
ዓለም አቀፍ የወንጌላውያን ተማሪዎች ኅብረት (IFES)፣ እ.አ.አ. በ1947 ዓ.ም. የተቋቋመ ነው። ተቋሙ በመቶ ስድሳ አገራት ላይ የሚገኙና ቊጥራቸው ስድስት መቶ ሺህ የሚደርሱ የወንጌላውያን ክርስትና አማኝ የሆኑ የከፍተኛ ትምህርት ተማሪዎችን በማስተባበር ላይ ሲሆን፣ ተማሪዎችን በወንጌል በመድረስ በጎ ተጽእኖ እንዲያመጡ የሚል ራእይ ሰንቆ የሚሠራ ዓለም አቀፍ አገልግሎት ነው፡፡ መቶ ሰማኒያ አምስት ሺህ የሚደርሱትን ተማሪዎች የሚያስተባብረው አሁን ዘላለም እንዲመራ ኀላፊነት የተሰጠው የአፍሪካው ቢሮ (EPSA) ነው፡፡
“Biblical Education By Extension (BEE World)” እና በዳላስ ያለችው የኢትዮጵያ ወንጌላውያን ቤተ ክርስቲያን በአጋርነት ሲያሠለጥኗቸው የነበሩትን ዐሥራ ሰባት የመጀመሪ ዙር ተማሪዎችን አስመረቁ።
የሕንጸት መጽሐፍ ክበብ ላለፉት ዐሥርት ዓመታት ሲያከናውናቸው የነበረውን ተግባር ለመዘከር የ10ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ሰኔ 4 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. ልዩ በሆነ መርሓ ግብር አከበረ። ክብረ
“የቤተ መጻሕፍት አደረጃጀት” የተሰኘ የግማሽ ቀን ሥልጠና ለተለያዩ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያናት ተወካዮች ተሰጠ። በሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ አዘጋጅነት የተዘጋጀው ሥልጠና፣ ቅዳሜ ሚያዚያ 14 ቀን፥ 2015 ዓ.ም. በላቭ ኤንድ ኬር ማዕከል የተካሄደ ነበር።
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.
Add comment