[the_ad_group id=”107″]

በመስከረም ወር ለውይይት ቀርቦ የነበረውና፣ “የተዓምራት አምላክ ታምረኛ” የተሰኘው ግለ ታሪክ መጽሐፍ ሁለተኛ ክፍል እንደሚከተለው ቀርቧል።

3 comments

Your email address will not be published. Required fields are marked *

  • ግምገማው በእለቱ ከነበረው ዝግጅት ብዙ ተቀንሶለት የቀረበ ይመስለኛል። 1/ ጥያቄ አቅራቢዎቹ ወንዶች ብቻ ናቸው! ሴቶችም ነበሩ እኮ! አንድ ከወንድ፣ አንድ ከሴት ማፈራረቅ ይገባል። አወያዩ ይህን ማድረግ ነበረበት፤ በተጨማሪ፣ ጥያቄዎቹ በትክክል አልተመለሱ ከሆነ መከታተል፣ በተሠነዘሩ ጥያቄዎች ላይ አክሎ በመጠየቅ ውይይቱን ማዳበር ይችል ነበር። 2/ ስለ መጽሐፍ ጥራት፣ ወዘተ፣ በአርታኢና በገምጋሚ መመኻኘቱ ተገቢ አይደለም። ኃላፊነቱ የመጽሐፉ ደራሲ ብቻ ነው፤ 3/ በመጽሐፉ ውስጥ የተነሡት ዋነኛ ጒዳዮች ሳይነኩ ቀርተዋል። ለወጣቶቹ አጥጋቢ ምላሽ የተሰጣቸው አይመስልም። ደራሲውና ገምጋሚው በጥያቄዎቹ ደስ እንዳላላቸው ከፊታቸው ያስታውቃል። ፕሮግራሙ፣ ግምገማን እንዴት ማካሄድ እንደማይገባ ጥሩ ማስተማሪያ ይሆናል እላለሁ። ደራሲና ገምጋሚ ወዳጆች መሆናቸው፣ ደራሲው ገምጋሚው እንዳደላለት ደጋግሞ መግለጡ ምርጫው ትክክለኛ እንዳልነበረ፣ ግምገማውም ግቡን እንዳልመታ ያረጋግጣል።

    ስለ መፃሕፍት መሠረታዊ መረዳት ያለው ሰው፣ መጽሐፉን አንብቦ፣ ደራሲውን በመጽሐፉ ይዘት፣ ውበት፣ የአሳብ ፍሰት፣ መያያዝ እና ጥራት፣ ወዘተ በታዳሚ ፊት መመርመር ነበር። ቀጥሎ አንብቦ ከመጣ ታዳሚ (ጊዜ ለመቆጠብ) በቅድሚያ ጥያቄ ተሰብስቦ (የተደጋገሙ ጥያቄዎች ተወግደው) ደራሲው ስብከት ባልመሰለ መልኩ እንዲመልሳቸው ማድረግ ነበር። የመጽሐፉ ዋጋ ውድ ከሆነ፣ አቅም ያላቸው ገዝተው፣ (ደራሲዎችም) በሥጦታ እንዲያበረክቱ መጠየቅና አቅም የሌላቸው አስቀድመው ተቀባብለው እንዲያነብቡት ማድረግ። በተጨማሪ፣ ይህን መሰል ፕሮግራሞችን፣ ሕዝብ ማስተማሪያ፣ እውቀት መገብያ እንጂ የግል ጒዳይ አለማድረግ ነው። መጽሐፍ ከመፃፍ ባልተናነሰ፣ ደራሲን አቅርቦ መጠየቅ ተጠያቂነትን ማነጽ ነውና። ለምን እንዲህ አልሽ? እዚህ ጋ እንዲህ ብለህ፣ እዚያ ጋ እንዲህ ማለትህ እንዴት ይታረቃል? ላልከው መረጃህ ምንድነው? ይኸ የኋለኛው ተዐማኒነትን መጠየቅ ነው፤ ያለተዐማኒነትማ ደራሲነት ውኃ በላው!

    • በቦታው ነበርኩ። በስልኬም ውጭ ላለ ወዳጄ ድምፁን ቀድቼ ልኬለት ነበር። ምንም ሴት ጠያቂ አልነበረም። እጄ ላይ ያልተቆራረጠ የሁለት ሰዓት ከአስራ ስምንት ደቂቃ ፋይል አለ ለማስረጃነት። ሕንጸቶችም የለቀቁትን አይቻለሁ። በመብራት መቆራረጥ ጊዜ የነብረውን ጊዜ፣ መጀመሪያ እና መጨረሻ ላይ ያሉትን ጸሎቶች ቆርጠዋል፤ እርግጥ ነው። የተሳታፊ ግን አልተቆረጠም።

      • ሴት ጠያቂ ነበረ ሳይሆን፣ ሴቶች ታዳሚዎች ነበሩ፣ እያፈራረቁ መጠየቅ ይሻላል የሚል መሰለኝ

SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.