ሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ

የሕንጸት የመጽሐፍ ክበብ፣ በክርስቲያን ማኅበረ ሰቡ ዘንድ የንባብና የውይይት ባሕል እንዲዳበርና ብርቱ ጸሐፊያን እንዲጎለብቱ በሚል በወር አንድ ጊዜ የሚደረግ የመጽሐፍ ግምገማ/ውይይት ያካሄዳል፡፡
በዚህም የሚከተሉትን ዝርዝር ዓላማዎችን ለማሳካት ይሠራል፡-

  • የንባብ ባሕል እንዲዳብር የበኩሉን ድርሻ መወጣት፤
  • ክርስቲያን ጸሐፊያን እንዲበራከቱ ማበረታታት፤
  • የሚታተሙ መጻሕፍት ደረጃቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ሒሳዊ ምልከታዎችን በማቅረብ ማገዝ፤
  • በክርስቲያን ማኅበረ ሰቡ መካከል የውይይት ባሕልን ማዳበር፤

ለግምገማ የሚቀርቡ መጻሕፍ ከሞላ ጎደል የሚከተሉት ይሆናሉ፡-

  • በዋናነት የወንጌል አማኝ ማኅበረ ሰቡን የሚመለከቱ ሆነው ሲገኙ፤
  • የመጻሕፍቱ ፋይዳ ጉልሕ ሆኖ ሲገኝና ይህም አሳማኝ በሆነ መልኩ መብራራት ሲችል፤
  • በተቻለ መጠን ደረጃቸውን የጠበቁና ʻሊነበቡ ይገባቸዋልʼ ተብለው የሚታመነባቸው ሥራዎች ሊሆኑ ይገባል፤
  • ጻሓፍቱ በአማኝ ማኅበረ ሰቡ ውስጥ ያላቸው ተደማጭነት ጉልሕ ሆኖ ሲገኝ ዕድል ሊሰጠው ይችላል፤
  • የወንጌል አማኝ ማኅበረ ሰቡን በክፉም ሆነ በደግ የሚመለከቱና በማናቸውም አካላት የተጻፉ ሥራዎች ሲገኙ፤
  • ወቅታዊና አንገብጋቢ በሆኑ ጉዳዮች ላይ የተጻፉ መጻሕፍት ሲኖሩ፤

 

ከላይ የተዘረዘሩት መሥፈርቶች በየትኛውም የሥነ ጽሑፍ ዘውግ ውስጥ ያሉትን መጻሕፍት ይመለከታል፡፡

ከዚህ በፊት የነበሩ የመፅሐፍ ቅኝቶች