[the_ad_group id=”107″]

ፍርሀት እና ምሕረት

ቴዎድሮስ ሲሳይ

በዚህ ዓለም ስንኖር፣ ጕዳያችንን እና ነገራችንን እንዴት እንደምንከውን ግድ የሚለን እና የሚያስጠነቅቀን የእግዚአብሐር ፍርሀት ነው። በእግዚአብሔር ፍርሀት እንወቀሳለን፣ እንገሠፃለን፣ እንከለከላለን፣ እንገደባለን፣ ጨርቃችንን ጥለን እንሮጣለን፣ ማቅ ለብሰን እናለቅሳለን፣ ፊታችንን ወደ እርሱ አዙረን እንመለሳለን። “ሰው ከሞት ወጥመድ ያመልጥ ዘንድ እግዚአብሔርን መፍራት የሕይወት ምንጭ ነው” እንደሚል ቃሉ (ምሳሌ 14፥27)።

ከሳትንበት፣ ከወደቅንበት፣ ከተወቀስንበት፣ ከተከሰስንበት ነጻ መውጫው መንገዱ ደግሞ የእግዚአብሔር ምሕረት ነው። ስለዚህም ነፍስ የመተላለፏን ወቀሳ በተቀበለች ጊዜ፣ በኀጢአቷም ምክንያት ኀፍረት በወደቀባት ጊዜ፣ ብቸኛውና ትክክለኛ ርምጃዋ መሆን ያለበት ወደ እግዚአብሔር ምሕረት መሸሽ፣ ወደ ጸጋው ዙፋኑም መቅረብ ነው። ትክክለኛ መንገዱም ይህ ነው፤ ከዚህ የተለየ ርምጃ ጥቅም የለውም። ወደ እግዚአብሔር ምሕረት ከሚወስደው የተለየው መንገድ  ከሥጋ ነው፤ ከዓለም ነው፤ ከሰይጣን ነው።

በእግዚአብሔር ፍርሀት ምክንያት፣ ነፍሳችን ኀፍረት ከሆነባት ነገር፣ ከኀዘን ወጥታ ወደ ዕረፍት የምትመጣው፣ የእግዚአብሔርን ምሕረት ስትቀበል ነው።

ፍርሀቱን ያወቀ፣ ምሕረቱንም ሊያውቅ ይገባል። ፍርሀቱን የተቀበለ፣ ምሕረቱን ይቀበል ዘንድ ይህ ይሰጠዋል። የእግዚአብሔር ምሕረት ያለ እግዚአብሔር ፍርሀት ምውት ነው፤ “ኀጢአት ያለ ሕግ ምውት ነውና” የሚለውን የጳውሎስን መሥመር ያስታውሷል።

ፍርሀቱን ያወቀ፣ ምሕረቱንም ሊያውቅ ይገባል። ፍርሀቱን የተቀበለ፣ ምሕረቱን ይቀበል ዘንድ ይህ ይሰጠዋል። የእግዚአብሔር ምሕረት ያለ እግዚአብሔር ፍርሀት ምውት ነው፤

ምሕረቱ ያለው፣ ፍርሀቱ ላለባቸው ነው። በእግዚአብሔር የማያምኑ፣ ፍርሀቱን የማያውቁ ወይም የናቁ፣ እነርሱ ምሕረቱን አያውቁም፤ አይቀበሉምም። የእግዚአብሔር ፍርሀት በእግዚአብሔር እምነት ምክንያት እንደ ሆነ ሁሉ፣ የእግዚአብሔር ምሕረትም እንዲሁ በእግዚአብሔር እምነት ይሆንልናል።

“እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበል በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።”— ዕብራውያን 4፥16

Tewodros Sissay

ቴዎድሮስ ሲሳይ፣ ነዋሪነቱን በምድረ አሜሪካ፣ ቴክሳስ ዳላስ ውስጥ ያደረገ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነው።

Share this article:

‘ምን ላስብ? ምንስ ላድርግ?’ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ

የወንጌል አማኝ ነኝ። የወንጌል አማኝ በመሆኔ ከክፉ ዳንኩ እንጂ ከዓለም አልወጣሁም። ከዓለም ወጥቼም ከሆነ፣ የወጣሁት ዓለማዊነት ከውስጤ ወጥቶ የወንጌል መልእክተኛ ሆኜ ወደ ዓለም እንድላክ እንጂ፣ የራሴን እና የብጤዎቼን ደሴት ሠርቼ፣ ተነጥዬ እንድኖር አይደለም። ጥበብ እንደ ጎደላት ሰጎን ጭንቅላቴን አሸዋ ውስጥ ቀብሬ ‘የለሁም’ ካላልኩ በስተቀር የአገሬ፣ የምድሬ ነገር ያገባኛል። ጥሪዬ ለምድር ጨውነት፣ ለዓለም ብርሃንነት እስከ ሆነ ድረስ ምድሩና ዓለሙ የሥራ መስኬ፣ የተግባር መከወኛዬ እንጂ ጥዬ የምሸሸው ጣጣ አይደለም። ያመንኩት የዓለምን መድኃኒት ነው፤ መድኃኒቱን ተቀብዬ መዳን ብቻ ሳይሆን መድኃኒት እንድሆን ተጠርቻለሁ። ስለዚህ ጥል ባለበት ፍቅርን፣ መለያየት ባለበት አንድነትን፣ ጥፋት ባለበት ልማትን፣ ኹከት ባለበት ሰላምን ለማወጅ ተጠርቻለሁ።

ተጨማሪ ያንብቡ

“ታሪካዊ” የተባለው የኅብረቱ ውሳኔ እና የተሰጠው ምላሽ

የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ኅብረት ጠቅላላ ጉባኤ፣ ከመጋቢት 21-22፣ 2009 ዓ.ም. ድረስ ባካሄደው 32ኛ መደበኛ ስብሰባው፣ በአስተምህሮ ዝንፈት፣ መጽሐፍ ቅዱሳዊ ባልሆኑ ልምምዶች እና በሞራል ውድቀት ላይ እጅግ ጠንካራ ነው የተባለለት የአቋም መግለጫ አወጣ፡፡ መግለጫው የወጣው በተጠቀሱት ጕዳዮች ላይ ኅብረቱ ያዘጋጀው ጥናት ለጠቅላላ ጉባኤው ከቀረበና ውይይት ከተካሄደበት በኋላ እንደ ሆነም ተነግሯል፡፡

ተጨማሪ ያንብቡ

Add comment

Your email address will not be published. Required fields are marked *

SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.