
መንፈስ ቅዱስ በታሪክ ውስጥ
በዘመናችን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ምስባኮች ላይ መንፈስ ቅዱስ የሚለው ስም መጥራት የተለመደ ቢሆንም፣ ሕዝበ ክርስትያኑ ስለ መንፈስ ቅዱስ ማንነት ጠንቅቆ ያውቃል ለማለት አስቸጋሪ ይመስላል። መንፈስ ቅዱስን አስመልክቶ ግልጽ አስተምህሮ ያለም አይመስልም። ለአንዳንዶች መንፈስ ቅዱስ ተአምራት ማድረጊያ ኀይል፣ እንዲሁም በጨርቅ ተደርጎ እና በጠርሙስ ታሽጎ የሚወሰድ ትንግርት መፍጠሪያ ሲሆን፣ ለሌሎች ደግሞ ማነቃቂያ እና ተሃድሶ የሚያመጣ እሳት ወዘተ. ነው።