ዕቅበተ እምነትና ውግዘት
“ውግዘት ከዕቅበተ እምነታዊ ሙግት ይልቅ፣ የሰፋ ጥናትና በእግዚአብሔር ቃል ላይ የተመሠረተ ተብራርቶ የሚቀርብ ግንዛቤና ግልጽነት ይፈልጋል።” ጆንሰን እጅጉ
[the_ad_group id=”107″]
“ውግዘት ከዕቅበተ እምነታዊ ሙግት ይልቅ፣ የሰፋ ጥናትና በእግዚአብሔር ቃል ላይ የተመሠረተ ተብራርቶ የሚቀርብ ግንዛቤና ግልጽነት ይፈልጋል።” ጆንሰን እጅጉ
“የዕቅበተ እምነት ሥራ የሁሉም አማኝ ድርሻ ቢሆንም፣ ትልቁን ሚና መወጣት ያለባቸው ግን ግለ ሰቦች ሳይሆኑ ቤተ ክርስቲያን ናት” አሌክስ ዘፀአት
በዘመናችን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ምስባኮች ላይ መንፈስ ቅዱስ የሚለው ስም መጥራት የተለመደ ቢሆንም፣ ሕዝበ ክርስትያኑ ስለ መንፈስ ቅዱስ ማንነት ጠንቅቆ ያውቃል ለማለት አስቸጋሪ ይመስላል። መንፈስ ቅዱስን አስመልክቶ ግልጽ አስተምህሮ ያለም አይመስልም። ለአንዳንዶች መንፈስ ቅዱስ ተአምራት ማድረጊያ ኀይል፣ እንዲሁም በጨርቅ ተደርጎ እና በጠርሙስ ታሽጎ የሚወሰድ ትንግርት መፍጠሪያ ሲሆን፣ ለሌሎች ደግሞ ማነቃቂያ እና ተሃድሶ የሚያመጣ እሳት ወዘተ. ነው።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቴሌቪዥን መስኮት ብቻ እናውቃቸው የነበሩ አንዳንድ አፍሪካውያን “አገልጋዮች” በአንድም ሆነ በሌላ መልኩ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መድረክ ላይ መታየት ጀምረዋል። በቅርቡ የተከሰቱ ሁለት ኩነቶችን እንኳ ብንመለከት “ሜጀር ሼፐርድ ፕሮፌት” ቡሽር ከማላዊ፣ “ነቢይ” ኮቦስ ቫን ሬንስበርግ ከደቡብ አፍርካ ወደ ኢትዮጵያ ያደረጉትን ጉብኝት ልብ ይሏል።
ባለፈው ዕትም የ“ነቢይ” ቡሽሪን የኢትዮጵያ አገልግሎት አስመልክቶ አንድ መጣጥፍ አቅርቤ ነበር፡፡ የእኚህ ሰው “አገልግሎት” በሐሰት የተሞላና ከመጽሐፍ ቅዱስ እውነት ጋር የሚጣረስ መሆኑን አሳይቻለሁ፡፡ እንዲህ ዐይነቱ የስህተት አስተምህሮ እንደ ቡሽሪ ባሉ ከውጭ ሀገር በሚመጡ አገልጋዮች ላይ ብቻ የሚታይ ሳይሆን በእኛ በኢትዮጵያዊያን ዘንድ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስፋት እየተስተዋለ የመጣ ችግር ነው፡፡ የዛሬው መጣጥፍ የትኩረት አቅጣጫም ይህ ይሆናል፡፡
የክርስትና እምነት ገና ከጅማሬው እውነተኛውን የክርስትናን አስተምህሮ በሐሰት ለመበረዝ በሚጥሩ የኑፋቄ ትምህርት መምህራን ከፍተኛ ተግዳሮት ይደርስበት እንደ ነበር ከመጽሐፍ ቅዱስን እንረዳለን፡፡ በአዲስ ኪዳን ውስጥ ከሚገኙ መጻሕፍት መካከል አንድ ሦስተኛውን ስፍራ የሚወስደው ለመናፍቃን ትምህርት የተሰጠ ምላሽ እንደ ሆነ በዘርፉ ምርምር ያደረጉ የሥነ መለኮት ምሁራን ይጠቁማሉ፡፡
በአንዳንድ የወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት እንዲሁም ሚኒስትሪ መሪዎችና አገልጋዮች ዙሪያ ያሉትን ድክመቶች አስመልከቶ ለየት ባለ ግልጽነትና ʻአሁንስ በዛʼ ብለው የተነሡ ይሆኑ? በሚያሰኙ ብዕሮች የተጻፉ የሚመስሉ ጠንከር ያሉ መልእክቶች በመጽሔቶች አማካይነት ብቅ ብቅ እያሉ ነው። ደስ ይላል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን በመሠረታዊ አቋሞቿ ላይ የአመለካከት ለውጥ እያመጣች እንደ ሆነ ይስተዋላል፡፡ ለውጡም ከእምነት ወደ ስሜታዊነት፣ ከተጨባጭ እውነት ወደ ሕልመኝነት እንዲሁም ከምክንያታዊነት ወደ ምሥጢር ናፋቂነት ዞራለች፡፡ ግን ለምን? ለምን በመጣው የትምህርት ንፋስ ሁሉ እንወሰዳለን? ለእነዚህ ጥያቄዎች መልሱ ዘርፈ ብዙ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ከእነዚህም ጥቂቶቹን ለማንሣት ያህል፡- እግዚአብሔርን ወደ መምሰል የሚያመራውን ንጹሕ የእግዚአብሔር ቃል ከማስተማር ይልቅ የራሳችንን ገድል በየምስባኩ ማውራታችን፣ ሕዝባችንን የክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ሳይሆን የግለ ሰቦች ተከታይ ማድረጋችን እንዲሁም አማኙ ማኀበረ ሰብ ከምንም ነገር በላይ የተኣምራት ናፋቂዎች እንዲሆን ማድረጋችንና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society is a faith-based society founded in June 7, 2013 by a group of Christians who are committed to the expansion and edification of the Evangelical Churches of Ethiopia. The Ge’ez word ‘Hintset’, which means ‘to edify’ or ‘to build’, is intended to describe this commitment.
“ከመልእክተ ሕንጸት” በስተቀር፣ በድረ ገጹ ላይ የሚቀርቡ ማናቸውም ዝግጅቶች የሕንጸት ክርስቲያናዊ ማኅበር አቋምን ላይወክሉ ይችላሉ።
With the exception of “Hintset’s Editorial”, any pubication presented on the Website may not necessarily represent the position of Hintset Christian Society.
Hintset Christian Society
Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.