[the_ad_group id=”107″]

አውራ ነገር

መለኮታዊ ፈውስና የእምነት ምስክርነት ፈተናዎች

በማርች 23 ቀን 2008 ዓ. እ. በአንድ የአሜሪካ ቤተ ሰብ ውስጥ አስደንጋጭ ኀዘን ተከሠተ። በማርች 26 ዜናውን ለመጀመሪያ ጊዜ ያሠራጨውን አሶሼትድ ፕሬስን ጨምሮ ዋነኛዎቹ የዜና ተቋማት ወሬውን ተቀባበሉት። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ፣ የዊስኮንሲን ነዋሪ ስለ ነበረችው የ11 ዓመቷ እምቦቃቅላ ማድሊን ካራ ኑማን (Madeline Kara Neumann) በተከታታይ መነገርና መጻፍ ተጀመረ። ክርክሩም ተጧጧፈ።

Read More »

እኔነት የሚፈታተነው የክርስቶስ ማኅበር አንድነት

“ደሞዛችን አልደረሰም እንዴ?” ስትል ጠየቀችኝ። ጠያቂዋ ሚስቴ ስትሆን፣ ትዳር ከመሠረትን ሁለት ሳምንት ገደማ የሆነን ይመስለኛል። ለካንስ ላቤን አንጠፍጥፌ የማገኘው ደሞዝ፣ ከትዳር በኋላ ደሞዛችን ሆኗል! ላቤም የግሌ አይደለም ማለት ነው። ይሄን ማሰቡ ድንጋጤ ለቀቀብኝ። ባልና ሚስት አንድ አካል፣ አንድ አምሳል እንደሆኑ አልጠፋኝም፤ ክርስቲያናዊው ትዳር፣ “ባል በገዛ ሥጋው ላይ ሥልጣን የለውም፤ ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ” በሚል…

Read More »

ጋሽ በቀለ ይናገራል

መጋቢ በቀለ ወልደ ኪዳን ለአብዛኞቹ አንባቢዎቻችን የምናስተዋውቃቸው ዐይነት ሰው አይደሉም። በአጭሩ ለዐርባ ዓመታት ያህል በዘለቀው አገልግሎታቸው፣ መጋቢ ከሆኑባት የኢትዮጵያ ሙሉ ወንጌል ቤተ ክርስቲያን ባሻገር ብዙዎቹን አብያተ ቤተ ክርስቲያናት፣ ከተማ ገጠር፣ አገር ቤት ውጪ አገር ብለው ያገለገሉ መሆናቸው፣ በወጣቱም ሆነ በቀደሙት ዘንድ ታዋቂ አድርጓቸዋል። ለዚህ ነው የምናስተዋውቃቸው ዐይነት ሰው አይደሉም ማለታችን። መጋቢ በቀለ በብዙዎች ዘንድ “ጋሽ በቄ” በሚል ስም ነው የሚጠሩት።

Read More »

ጴንጤቆስጣዊ – ካሪዝማቲካዊ

የኢትዮጵያ ወንጌላዊው ክርስትና ካሪዝማዊነት እና ጴንጤቆስጣዊነት ዐይነተኛ መለያው ይመስላል። በአመዛኙ በልምምድ ላይ ትኩረቱን ያደርጋል እየተባለ የሚወቀሰው ይህ ክርስትና፣ ወደ ኢትዮጵያ የመጣበትን ታሪካዊ አጎለባበትና ያመጣውን ትሩፋት እንዲሁም አሁን እየተፈተነበት ያለበትን ዐደጋ ሚክያስ በላይ እንደሚከተለው ያስቃኛል።

Read More »

ጕራማይሌው የቴሌቪዥን አገልግሎት

ይህ ያለንበት የ21ኛው ክፍለ ዘመን የአስተሳሰብና የባህል ሽግግር/ለውጥ እጅግ በጣም ፈጣን የሚባል ነው፡፡ እንደ ከዚህ ቀደሙ በአንድ አካባቢ ያሉ አስተሳሰቦች፣ ፍልስፍናዎች፣ ሃይማኖታዊ ተዋስኦዎች፣ ወዘተ. ወደ ሌላው አካባቢ ለመድረስ ዓመታትን፣ ምናልባትም ዘመናትን የሚያስቆጥሩበት ረጅሙ ጊዜ አሁን አጥሯል፡፡ ለዚህ የተለያዩ ምክንያቶች ቢሰጡም፣ የብዙኀን መገናኛ ሚና ግን ጉልሕ ሥፍራ የሚይዝ እንደ ሆነ ከብዙዎች የተሰወረ አይደለም፡፡

Read More »

ፍትሕ ወይስ ምሕረት

ጸሐፊ፣ ተመራማሪ እና አስተማሪ የሆነው ምኒልክ አስፋው ከሚኖርበት አሜሪካ ሆኖ ስለ ፍትሕ እና ምሕርት/ይቅርታ ባዘጋጀው ጽሑፉ የዚህ ዕትም ዋና ርእሰ ጉዳይ ጸሐፊ ሆኖ ቀርቧል። ጽሑፉ በዋናነት ከፍትሕ እና ከምሕረት የትኛው የበለጠ ፋይዳ ያለው መሆኑን በመጠቆም የተሰናዳ ነው። ምኒልክ ለዚህ መነሻ የሚያደርገውም እውቁን የቀድሞ የደቡብ አፍሪካ ፕሬዚዳንት የነበሩትን ሟቹ ኔልሰን ማንዴላን ነው። እንደ እርሱ እምነት ከሆነ የማንዴላ የዕርቅ መንገድ በቅራኔ ለተሞላ ኅብረተ ሰብ ዐይነተኛ ምሳሌ ነው። ትልቅነት የሚለካውም ይቅር በሚሉና ምሕረት በሚያደርጉ ሰዎች የሕይወት ፈለግ መሆኑንም ይሞግታል።

Read More »

የነገረ መለኮት ነገር

ክርስትና በአፍሪካ ውስጥ በስፋት በመስፋፋት ላይ እንደ ሆነ የተለያዩ ጥናቶች ይጠቁማሉ። ሆኖም ግን ʻእየተስፋፋ ያለው ክርስትና ምን ዐይነት ገጽታ አለው?ʼ የሚለው ትኩረት የሚያሻው ጥያቄ ነው። የቁጥር ዕድገት ቤተ ክርስቲያን በማኅበረ ሰቡ ውስጥ ያላትን መገኘት በማግዘፍ የሚኖራትን ሚና ያጎላዋል። በተመሳሳይ መልኩ ደግሞ ዕድገቱ የተለያዩ ተግዳሮቶችን ይዞ ይመጣል። ቤተ ክርስቲያን እነዚህን ዕድሎች የማትጠቀም ወይም ለተግዳሮቶች ምላሸን የማትሰጥ ከሆነ በምትኖርበት ማኅበረ ሰብ ውስጥ ያላት ፋይዳ እጅግ አናሳ ይሆናል።

Read More »

ልዩ ወንጌል

በሕንጸት ቁጥር 1 ዕትም፣ በአውራ ነገር ዐምድ ሥር “የወንጌላውያኑ መንታ መንገድ” በሚል ሐተታዊ ጽሑፍ ተስተናግዶ ነበር፡፡ ጽሑፉ በዋናነት ከመቶ ዓመታት በላይ ዕድሜ ያስቆጠረው የወንጌላውያን ክርስትና በኢትዮጵያ ይዟቸው ስለመጣው ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ለውጦች በማተት፣ አማኝ ማኅበረ ሰቡ ስላበረከታቸው በጎ አስተዋጽዖዎች በመጠቆም ላይ ያተኮረ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ይህንን በጎ ተጽእኖውን ማስቀጠል በማይችልበት ደረጃ ላይ እንደደረሰና ለዚህም ምክንያቱ ልዩ የሆነ አስተምህሯዊ አቋምና ልምምድ በቤተ ክርስቲያን መተዋወቁ እንደ ሆነ ይጠቁማል፡፡ ይህ ልዩ አስተምህሮና ልምምድ ደግሞ በ“እምነት እንቅስቃሴ” ወይም በ“ብልጽግና ወንጌል” የተጠመቀ “ክርስትና” ወደ አማኝ ማኅበረ ሰቡ መዝለቁ ነው፡፡

Read More »

የወንጌላውያኑ መንታ መንገድ

የኢትዮጵያ ወንጌላዊው ክርስትና በአገሪቱ ከመቶ ዓመታት በላይ አስቆጥሯል፡፡ በተለያዩ ውጣ ውረዶች ውስጥ ያለፈው ይህ ሃይማኖታዊ ማኅበረ ሰብ በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ብሎም ፖለቲካዊ መስተጋብር ውስጥ የራሱን አሻራ እየተወ የመጣ መሆኑን መካድ አይቻልም፡፡ ይልቁኑም ደግሞ በአሁኑ ጊዜ እንደ ከዚህ ቀደሙ የተናቀ ማኅበረ ሰብ ሆኖ ላለመቀጠል በሚያደርገው ትግል እየተፈጠረ ያለው ለውጥ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ነው፡፡ ባለፉት ዐሥርት ዓመታት የተከሰተው ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያ ለውጥ በአገሪቱ ሃይማኖታዊ መስጋብር ላይ የራሱ የሆነ ተጽእኖ አሳድሯል፡፡ በዚህ ለውጥ ውስጥ ተጠቃሚም ተጎጂም መኖሩ አይቀርም፡፡ በአንዳንዶች ዘንድ ይህ ለውጥ ለወንጌላውያኑ ማኅበረ ሰብ የድል ብሥራት ይዞ እንደመጣ ሊታሰብ ይችላል፡፡ በርግጥ ይህ አስተሳሰብ እውነት የሚሆንባቸው ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላል፤ በአንጻሩም ያልተጠበቀ ውጤት አስከትሎ እንደ ሆነ ማሰቡ ተገቢ ነው፡፡

Read More »
SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.