የበዓለ ጥምቀት አከባበር በግብጽና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት
ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላደረገው ነገር ኹሉ የመታሰቢያ በዓል አዘጋጅቶ አምላክ የኾነው እርሱ ሰው በመኾን ያሳየውን ድንቅና በትሕትና የተሞላ ሥራውን በመዘከር እርሱን በእውነተኛ ልብ ማምለክና ማክበር መቻል መልካም ነገር ነው። ትልቁ ጥያቄ ግን በዚህ ውስጥ የበዓሉን ባለቤት ስንቱ ሰው አስታውሶት ይኾን?