[the_ad_group id=”107″]

ከኦርቶዶክስ አምባ

የበዓለ ጥምቀት አከባበር በግብጽና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት

ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላደረገው ነገር ኹሉ የመታሰቢያ በዓል አዘጋጅቶ አምላክ የኾነው እርሱ ሰው በመኾን ያሳየውን ድንቅና በትሕትና የተሞላ ሥራውን በመዘከር እርሱን በእውነተኛ ልብ ማምለክና ማክበር መቻል መልካም ነገር ነው። ትልቁ ጥያቄ ግን በዚህ ውስጥ የበዓሉን ባለቤት ስንቱ ሰው አስታውሶት ይኾን?

Read More »

የትንሣኤው ዐዋጅ

ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ መነሣቱ የሚታሰብበት የትንሣኤ በዓል በክርስቲያኖች ኹሉ ዘንድ በምስጋናና በዝማሬ በታላቅ ድምቀት ይከበራል። በኢኦተቤ ትውፊት መሠረት ከዘጠኙ የጌታ ዐበይት በዓላት መካከል አንዱና ታላቁ በዓል የትንሣኤ በዓል ነው። በቤተ ክርስቲያኒቱ ምእመናን ዘንድ በዓሉ አስቀድሞ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የጾመውን ጾም በማሰብና በመጾም፥ በመጨረሻም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለድኅነተ ዓለም በአይሁድ እጅ የተቀበለውን መከራና ሥቃይ የሚያስታውሰውን ሰሙነ ሕማማት (የሕማማት ሳምንት) በማስቀደም፥ በመጨረሻም ሞትን ድል አድርጎ የተነሣውን ጌታ በዝማሬዎች በመወደስና ትንሣኤ ክርስቶስን በማወጅ ይከበራል። ልዩ ልዩ ሃይማኖታውያንና ባህላውያን ሥነ ሥርዐቶችም የበዓሉ አካላት ናቸው።

Read More »

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና ሀብታተ መንፈስ ቅዱስ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን ስለምትቀበል፥ በውስጡ የሚገኙትን መልእክቶችም ትቀበላለች። ሀብታተ መንፈስ ቅዱስ (የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች) በመጽሐፍ ቅዱስ የተመዘገቡና ለቤተ ክርስቲያን ጥቅምና መታነጽ የተሰጡ ናቸው (ሮሜ ፲፪፥፮- ፰፤ ፩ቆሮ. ፲፪፥፬-፲፩)። ቤተ ክርስቲያኒቱ ሀብታተ መንፈስ ቅዱስን የምትረዳበት፥ የምትተረጕምበት፥ የምታስተምርበትና የምትለማመድበት መንገድ የተለየ ነው።

Read More »

ወርኀ ጽጌ ወስደት

“ወርኀ ጽጌ ወስደት” የተሰኘው ይህ ጽሑፍ፣ በወንጌላውያኑ ዘንድ ብዙ ትኩረት ስለማይሰጠውና ጌታ ኢየሱስ በሕጻንነቱ ወራት ከእናቱ ማርያምና ከዮሴፍ ጋር ወደ ግብፅ የተሰደደበትን ታሪክ መነሻ በማድረግ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስለ ሁነቱ ያለውን ትርክት ያስቃኛል።

Read More »

የአብርሃም እንግዶች እነማናቸው?

እውነተኛ ገጠመኝ ነው። ከኹለት ዐሠርት ዓመታት በፊት ታቦተ ሥላሴ ደባል[1] በኾነበት በአንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለሐምሌ ሥላሴ ክብረ በዓል የተገኙት ምእመናን በቍጥር ጥቂት ነበሩ። ይህን የታዘቡትና በሥልጣን በመናገር የሚታወቁት የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በኹኔታው ዐዝነው እንዲህ ብለው ነበር፤ “ምእመናን ዛሬ የሥላሴ በዓል እኮ ነው? ምነው ታዲያ ምእመናኑ ጥቂት ኾኑ? ይህን ጊዜ የገብርኤል በዓል ቢኾን እንኳን ለዓመቱ ለወሩም ብዙ ሕዝብ ይገኝ ነበር፤ ምእመናን ከገብርኤል እኮ ሥላሴ ይበልጣሉ? ስለዚህ ማንን ማምለክ እንዳለብን ማስተዋል ይገባናል።”

Read More »

በዓለ ጰራቅሊጦስ

በኢትዮጵያ ከ1555-1585 ዓ.ም. የነገሠው የዐፄ ሠርጸ ድንግል ዜና መዋዕል ጸሐፍት ዜና መዋዕሉን መጻፍ የጀመሩት የሚከተለውን ጸሎት በማቅረብ ነበር። “ኦ እግዚእየ ኢየሱስ ክርስቶስ አስተብቍዖ ወሰአሎ ለእግዚአብሔር አቡከ ከመ ይፈኑ ላዕሌነ ጰራቅሊጦስሃ መንፈሰ ጽድቅ ዘኢይክል ዓለም ነሢኦቶ። ወመጺኦ ውእቱ ይመርሐነ ኀበ ኵሉ ጽድቀ ነገር። እስመ አይነግር እም ኀቤሁ ፈጠራ ወሐሰት አምሳለ ካልኣን መናፍስት እለ አልቦ ጽድቀ[ቅ] ውስተ አፉሆሙ። – ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ዓለም ሊቀበለው የማይችለውን የእውነት መንፈስ የኾነውን ጰራቅሊጦስን ይልክን ዘንድ የባሕርይ አባትኽን እግዚአብሔርን ማልደው፤ ለምነውም። መጥቶም ወደ እውነት ነገር ኹሉ ይመራናልና፤ በአፋቸው ውስጥ እውነት እንደሌላቸው እንደ ሌሎች መናፍስት የሐሰትን ነገር ከራሱ አንቅቶ አይናገርምና” (የዐፄ ሠርጸ ድንግል ዜና መዋዕል 1999፣ 3)።

Read More »

ዘመነ አስተርእዮ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዓመቱን በወቅቶች ከፋፍላ፥ በዚያ ላይ የተመሠረቱ መዝሙሮችን በግእዝ ለእግዚአብሔር በማቅረብና ድንቅ ሥራውን በመዘከር ትታወቃለች። ለዚህም በስድስተኛው ምእት ዓመት የተነሣው የዜማ ደራሲ ቅዱስ ያሬድ ከብሉያትና ከሐዲሳት (ከመጽሐፍ ቅዱስ)፣ ከሊቃውንትና ከመሳሰሉት መጻሕፍት ለምስጋናና ለጸሎት የሚስማሙ ንባባትን በመውሰድና ለዜማ ተስማሚ በማድረግ፥ በአራቱ ክፍላተ ዘመን እንዲነገሩ ማዘጋጀቱን የዜማ ሊቃውንት ያስረዳሉ (ጥዑመ ልሳን /ሊቀ ካህናት/ 1981፣ 28)። አራቱ ክፍላተ ዘመን የተባሉትም በዓመት ውስጥ የሚገኙት አራቱ ወቅቶች ናቸው፤ እነርሱም መፀው (ወርኀ ጽጌ ዘመነ ጽጌ/አበባ)፣ ሐጋይ (በጋ)፣ ጸደይ (በልግ) እና ክረምት ሲኾኑ፣ አኹን የምንገኘው ከአራቱ ክፍላተ ዘመን ኹለተኛው ክፍል በኾነው በበጋ (ሐጋይ) ላይ ነው።

Read More »
SIGN UP FOR OUR NEWSLETTER.

Hintset’s latest news and articles of the week to encourage, challenge, and inform you.